Author name: admin

ትምህርተ ሥላሴ እና የቤተክርስቲያን ታሪክ

የመጽሐፍ ዳሰሳ [1] በመጀመሪያ ይህን ክፍል ለማጥናት ምሥጢረ ስላሴ ምን ማለት ነው!? የትምህርተ ሥላሴ ቀዳማይ አመንጪ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። አንዳንድ ሥላሴን ስሩን ሳይዙት አውቀን ጨርሰናል በማለት ሲናገሩ አስተውያለሁ በዕውነቱ ያሳዝናል ለዚህም ነው በተለይ በአባቶች መምህራን የምሥጢረ ሥላሴ   በስፋቱና በትልቅነቱ ሲነገርም እንዲህ ይባላል፦ “..ምሥጢረ ሥላሴን ጠልቆ ለማወቅ መሞከር ባሕረ ውቅያኖስን በዕንቁላል  እየቀዱ ለመጨረስ እየጨለፉም ለመጨለጥ እንደ ማሰብ ነው ይላሉ…” እውነት ነው፤ ለሰው ከተሰጡ ስራዎች ምሥጥረ ሥላሴን ከመመርመር የሰፋና እና የከበደ የለም። ➝ ሆኖም ስለ ሥላሴ በትክክል ማሰብ ለክርስቲያናዊ ኑሮ ዋንኛ ነገር መሆኑን አንባቢ ልብ ይበል። አይሁድ፣ ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች አንድን አምላክ ሲያመልኩ፥ የሥላሴን ትምህርት በአንድ አምላክ ከሚያምኑ ሌሎች ሁሉ ክርስቲያኖች ይለዩዋቸዋል። ስለዚህ ክርስቲያን ለራሱ ብቻ ሳይሆን የራሱን እምነት ለሌሎች ለመግለጥም የሥላሴን ትምህርት ማወቅ ይገባዋል። ➝ሥላሴ የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስአይገኝም። በግእዝ ቋንቋ ቃሉ ሦስትነት ማለት ነውና በትምህርተ መለኮት ጥቅም ላይ ሲውል..በአንዱ እግዚአብሔር ሦስት አካላት እንዳሉ ያሳስባል። በ2ኛው መቶ ዓመት የአንጾኪያ ጳጳስ የነበረው ቴዎፍሎስ በግሪክ ቋንቋ ትሪአስ እና ጠርጡሊያን በላቲን ቋንቋ ትርንታስ በእንግሊዘኛው ደግሞ TRINITY የሚለው ሲሆን፣ ቃሉ “Tri” ወይም “ሦስት” እና “Unity” ወይም “ኅብረት/አንድነት” ከሚሉት ሁለት የላቲን ቃላቶች የመጣና አንድ ቃል ሆኖ በተገናኝ የሚነበብ (“tri” + “unity” ) ነው። ሥላሴ የሚለው ቃልና ትምህርቱ እንደ መነጥር ሆነው በመፅሐፍ ቅዱስ ያለውን ትምህርት ጉልሕ ሆኖ እንዲታየን ያደርጋሉ እንጂ በእግዚአብሔር ቃል ላይ አዲስን ትምህርት አይጨምሩም። ትምህርተ ሥላሴ ለክርስቲያን ረቂቅ ፍልስፍናም አይደለም። ወደፊት እግዚአብሔር ቢፈቅድ ሥላሴን በደንብ እንመረምራለን። ወደ ዋናው ርዕሳችን ወደ ሚያንደረድር ሀሳብ ስንመለስ፦ ትምህርተ ሥላሴ እንደ አርዮስ ያሉ የመናፍቃን ጥቃት በቤተክርስቲያን ላይ ሲያደርሱ የመጠበቁ ሂደት ውስጥ ትልቅ ድርሻ ከነበራቸው አትናቴዎስ(Athanasius) አንዱ ቢሆንም ርእሰ ጉዳዩን በዳበረ መልኩ የተነተኑት ቀጰዶቃውያን አበው ናቸው። በመጀመሪያ ከዛ በፊት ቀጰዶቃውያን አበው እነማን ናቸው የሚለውን በጥቂቱ እንመልከት… ቀጰዶቃውያን አበው(Cappadocian Fathers) የሚባሉት ውስጥ፦ ትምህርተ ሥላሴ በቤተክርስቲያን ታሪክ ቅድመ ጉባኤ ኒቂያ አበው ግንዛቤአቸው ምን ነበር? ከላይ እንዳየነው ሥላሴ የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን ባይገኝም ትምህርተ ሥላሴ የነገረ መለኮት ዐብይ ርዕስ መሆኑን አይተናል። የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ምን ያህል ትምህርተ ሥላሴን እንደተረዱት ባናውቅም ግን፥ እግዚአብሔር ሦስት አካላት እንዳሉ አምነው የመለኮትን አንድነትንና የአካል ሦስትነትን ለትምህርታቸው መሠረት አደረጓቸው። የትምሕርተ ሥላሴ ቀዳሚ አመንጪ መጽሐፍ ቅዱስ ቢሆንም፣ በሐዋሪያት እግር ስር የተማሩ ቀደምት የሆኑ የቤተክርስቲያን አበው ምን አሉ የሚለውን ጉዳይ መቃኘት፣ የተዛባ የታሪክ መረጃ ያላቸው ሰዎችን ለማቅናት ጠቃሚነት ስላለው ይህ ጽሑፍ ዳሰሳዊ ጥናት ስለሆነ የሁሉንም አበው እማኝነትና ትምህርት በክፍል አንድ በስፋት ማቅረብ ስለማይቻል በተወሰነው እንመለከታለን። 1) ጶሊቃርጶስ (Polycarp) :- በ70ዓ.ም ተወልዶ በ155 ዓ.ም ወይም በ160 ዓ.ም የሞተ፣ የሐዋሪያው ዮሐንስ ደቀ መዝሙር የነበረ እንዲሁም የሰምርኔስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት የነበረ ሰው ነው።..ይህ ሰው ትምህርተ ሥላሴን በተመለከተ እንዲህ ብሏል፦ “ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር ሆይ…ዘላለማዊና ሰማያዊ በሆነ ሊቀ ካህናት በምትወደውና ባከበርኸው ልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለአንተና ለእርሱም እንዲሁም ለመንፈስ ቅዱስ አሁንም ሆነ ለዘላለም ክብር ይሁን”[2] 2) ዮስጦስ ሰማዕት (Justin Martyr) ፦ የቤተክርስቲያን አቃቤ እምነት የነበረና የሰማዕትነትን ክብር የተቀናጀው ይህ አባት አባት በ100 ዓ.ም ተወልዶ በ165 ዓ.ም እንደ ሞተ ይገመታል። ይህ አባት ትምህርተ ሥላሴን በተመለከተ እንዲህ ብሏል፦ “የዓለማት ጌታ በሆነው በእግዚአብሔር በስመ አብ፣ በመድሐኒታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ በውሃ መታጠብን ያገኛሉ”[3] 3)አግናጢዮስ ዘአንጾኪያ (Ignatius of Antioch) ፦ የአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት የነበረና በ98 ዓ.ም ወይም በ117 ዓ.ም እንደሞተ የሚገመት ክርስትናን ከመናፍቃን በመከላከሉ ዙሪያ ብዙ የጻፈ ዐቃቤ ክርስትና ነው። እንዲህም አለ፦ “በእምነትና በፍቅር፤ በወልድ፣ በአብና በመንፈስ ቅዱስ፤ በመጀመሪያው እና በመጨረሻው፤ ከሚያስደንቅ ጳጳስችሁ ጋር እናም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ካሉ ዲያቆናት ጋር በሚገባ በጠበቀ መንፈሳዊ አክሊል የምታደርጉትን ሁሉ በስጋና በመንፈስ እንዲከናወን በጌታችንና በሐዋርያት ትምህረት እድትጸኑ አጥኑ። ክርስቶስ ኢየሱስ ለአብ በስጋው እንደተገዛለት እናም ሐዋርያት ለክርስቶስ፣ ለአብና ለመንፈስ ቅዱስ እደሚታዘዙ እናንተም ለጳጳሳችሁ እና እርስ በእርሳችሁ ተገዙ(ታዘዙ) በዚያን ጊዜ በስጋችሁም በመንፈሳችሁም አንድነት ይኖራችኋል።”[4] 4) ጠርጡሊያኖስ ወይም ተርቱሊያኖስ (Tertullian 160-215) ፦ አፍሪካዊ ዕቃቤ ክርስትና እንዲሁም የነገረ መለኮት ሊቅ ነው። ክርስትናን ከመናፍቃንና ከሌሎች ሐያስያን ለመከላከል ብዙ ጽፎአል፦ “አብና ወልድ ሁለት ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ደግሞ ሦስት መሆናቸውን እንገልጻለን። የቁጥሩንም ቅድመ ተከተል ከድነት አንጻር ነው….ይህም አንድነትና ሦስትነትን መሠረት አድርጎ ሦስቱንም ማዕከል ያደረገ ነው፤ እነርሱም አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ። [አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ] ሦስት ናቸው….ነገር ግን በባሕርይ ሳይሆን በገጽ፣ በኀይል ሳይሆን ነገር ግን በዐይነት። በባሕርይና (Substance) በኀይል አንድ ናቸው፤ ምክንያቱም አንድ አምላክ ብቻ ስላለና ይህም ባሕርይ፣ ገጽና ዐይነት በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ዙሪያ ያለ በመሆኑ”[5] 5) አርጌንስ (Origen 185-254) ፦ የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን የነገረ መለኮት ምሁር ነው። አርጌንስ ክርስትናን በተመለከተ ብዙ የጻፈ ነው፦ “የእግዚአብሔር ቃል ወይም የእግዚአብሔር ጥበብ ጅማሬ አለው የሚል ማንኛውም ሰው፣ ቢያንስ እግዚአብሔርን መናቁ እንደሆነ ልብ ሊለው ይገባል…ምክንያቱም እግዚአብሔር ባለፉት ዓመታት ሆነ ዘመናት ከዚህ ውጪ ሊገመት በሚችልበት ጊዜ ሁሉ፣ እግዚአብሔር የጥበብ ባለቤት ነውና ይህ እውነት ለእግዚአብሔር አብ እንደሆነው ሁሉ ለወልድም ነው”[6] “እውነታው ይህ ከሆነ [መንፈስ ቅዱስ አሁን እንደ ሆነው ሁሉ ዘላለማዊ ካልሆነ፣ በዘመናት ውስጥ ዕውቀትን ገብይቶ መንፈስ ቅዱስን መሆን ከቻለ] መንፈስ ቅዱስ ለዘላለም ዓለም መንፈስ ቅዱስ መሆን ካልቻለ፣ እንደማይለወጠው አብና እንደ ልጁ ሁሉ መንፈስ ቅዱስ የሥላሴ አንዱ አካል ነው ማለት አይቻልም”[7] “የመለኮት ምንጭ ብቻ ሁሉን ነገር በቃሉና በምክንዩው የሚይዝ ከሆነ፣ በሥላሴ አካላት ውስጥ መበላለጥ ወይም መተናነስ የለም”[8] ሔሬኔዎስ(Irenaeus)፦ በ115 ዓ.ም ተወልዶ 190 ዓ.ም ሞተ፣ በልጅነቱ የሐዋርያው ዩሐንስ ደቀ መዝሙር ከነበረው ከጶሊቃርጶስ እግር ሥር የተማረ እንዲሁም የልዮን ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት የነበረ ሰው ነው፦ “ቤተ ክርስቲያን በዓለም ሁሉ እንዲሁም እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ብትበተንም፣ ቤተ ክርስቲያን ከሐዋርያትና ከእነርሱ ደቀ መዛሙርት የተቀበለችውን የሚከተለውን መሠረተ እምነት ነው፦…..ሁሉን ቻይ የሆነ እና ሰማይንና ምድርን እንዲሁም ባሕርን በእነዚህም ውስጥ የሚኖሩትን ሁሉ የፈጠረ አንድ እግዚአብሔር፤ በእግዚአብሔር ልጅ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ፣ ለድነታችን ሲል ትስብእት የሆነ፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ የእግዚአብሔርን ዘመን በነብያቱ ያበሠረ እንዲሁም የተወዳጁ ጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምጽአት፣ ከድንግል መወለድ፣ ሕማም፣ ከሙታን መነሣት፣ በአካለ ሥጋ ወደ ሰማይ ማረግ፣ “ሁሉን አንድ አድርጎ ለመሰብሰብ በአብ ክብር ከሰማይ መገለጥ፣ የሰው ልጆችን ሁሉ በአዲስ አካል ከሙታን ማስነሳት፣ ይኸውም ክርስቶስ ኢየሱስ ጌታችንና አምላካችን እንዲሁም አዳኛችንና ንጉሣችን መሆኑን፣ በማይታየው አብ ፈቃድ “በሰማይና በምድር ከምድርም በታች” ያለ ጉልበት ሁሉ እንዲበረከክለት፣ ምላስም ሁሉ ኀጢአት ብሎ እንደ ተሰዋ እንዲመሰክርለት ነው…”[9] ከጉባኤ ኒቂያ በፊት እንዲህ አይነት እምነት ያላቸው ከሆነ፣ የአስተምሮው ቀዳማይ አመንጪ ጉባኤ ኒቂያ ነው የሚባል ነገር ፈፅሞ የለም። ከሁሉ በፊት የሌለ በኒቂያ ነው የሥላሴ ትምህርት የተጀመረው ቢባል እንኳን ክርስቲያኑ ማህበረሰብ ከቀድሞው አስተምሮው ጋር የማይጣጣም ነው በሚል ተቃውሞ ለምን አላቀረበም? ለምንስ አላወገዘም? ኖሮስ ካለ ለምን በታሪክ ተዘግቦ አልተገኘም!? እነዚህን ከዚህ መጽሐፍ ዳሰሳ ካየን በተጨማሪ ጥናት ደግሞ በክፍል ሁለት ተመሳሳይ ሙግት አንስተን በጠርጡልያኖስ ላይ የሚነሱትን ሙግቶች የምንዳስስ ይሆናል። ማጣቀሻ 1] ትምህርተ ሥላሴ መሠረታውያን በዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ 2] Martyrdom of Polycarp, 14. ANF, I:42. 3] Justin, First Apology, LXI. ANF, I:183. 4] Epistle to the Magnesians, Chapter 13 5] Tertullian, Against Praxeas, 2. PL 2.156–57.፣ በቅንፍ ያለውን አይጨምርም። 6] De Princ. 1.2.; PG 11.132). 7] Alexander Roberts and James Donaldson, eds., The Ante-Nicene Fathers, Grand

ትምህርተ ሥላሴ እና የቤተክርስቲያን ታሪክ Read More »

ማርያም የሐሩን እህት?

“የእንበረም(አምራም/עַמְרָם) ሚስት ስም ዮካብድ(ዮኬቬድ/יוֹכֶבֶד) ነበረ። እርስዋ በግብፅ ከሌዊ የተወለደች የሌዊ ልጅ ነበረች፤ ለእንበረምም አሮንንና(አኻሮን/אַהֲרוֹן) ሙሴን(ሞሼኽ/מֹשֶׁה) እኅታቸውንም ማርያምን(ሚርያም/מִרְיָם) ወለደችለት።”— ዘኍልቁ 26፥59 በመጽሐፍ ቅዱሳችን መሰረት የአሮን (አኻሮን/אַהֲרוֹן)፣ የሙሴና(ሞሼኽ/מֹשֶׁה) የነብይቷ ማርያም(ሚርያም/מִרְיָם) አባታቸው እንበረም(አምራም/עַמְרָם) ነው።እንበረም በእብራይስጡ አምራም/עַמְרָם በ ፊደል ሜም “ם” ሲያበቃ በአረበኛው መጽሐፍ ቅዱስ ላይ አምራም(عمرام) በፊደል ሚም(م) የሚጨርስ ቃል ነው፦ أبْناءُ عَمْرامَ هُمْ هارُونُ وَمُوسَى وَمَرْيَمُ የእንበረምም ልጆች አሮን፥ ሙሴ፥ ማርያም።”— 1 ዜና 6፥3በቁርአኑ ላይ ደግሞ ኢምራን(عمران) በፊደል ኑን(ن) በሚያበቃ ስም ተጠቅሶ እናገኘዋለን[¹]። ذكر نسب موسى بن عمران (የአት-አጠበሪ ታሪክ ቅጽ3) ቀዓት(ቀኻት/קְהָת) ልጅ የሆነው  እንበረም(1 ዜና 6፥2) የመጀመሪያ ልጁ ነብይቷ ማርያም ስትሆን ሙሴ እና ወንድሙ አሮን የተወለዱት 1400-1500 ዓ.ዓ እንደሆነ ይታሰባል[²]። ከዚህ ሁሉ ዘመናት በኋላ በዘመነ አዲስ ኪዳን ጊዜ የጌታችንና የመድኃኒታችን እናት የሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም ኢየሱስን እንደወለደች ቅዱሱ መጽሐፋችን ይነግረናል። መጽሐፍ ቅዱስ የቅድስት ድንግል ማርያምን አባትና እናት ባይጠቅስልንም ብዙ ድርሳናትና ታሪካዊ መጽሐፍት ኢዮአቄም(Joachim) እና አና(Anne) እንደሆኑ ይነግሩናል[³]።ባጭሩ የሙሴ እህት ነብይቷ ማርያም ጺን ምድረ በዳ እንደሞተች በኦሪት ዘኍልቁ ም.20 ቁ.1 ላይ እንመለከታለን። ቅድስት ድንግል ማርያም ከሙሴ እህት ማርያም ጋር በማንነት ሆነ በነበሩበት ጊዜ ይለያያሉ። እንደዚህ ያክል የመጽሐፍ ቅዱሱን በንጽጽራዊ ትንተና ከተመለከትን ወደ ቁርአኑ እንለፍና የመሐመድን በታሪክ ላይ የፈጸመውን ወንጀል እንመልከት፦መሐመድ በቁርአኑ ላይ የኢሳ እናት ማርያምን እና የነብዩ ሙሴ እና የአሮን እህት ማርያምን እንደ አንድ ሴት አድርጎ ማስተማሩ ነው!!!የብዙ ዘመናት ልዩነት ያላቸው በሁለት ታሪኮች መካከል ያለ መመሳሰልን ማለትም፦ ➙ የሙሳ ወንድም ሃሩን እና የኢሳ እናት ወንድም ሃሩን ➙የሙሳ አባት ኢምራን እና የኢሳ እናት አባት ኢምራን ➙ ራሷ ባለ ታሪኳ የኢሳ እናት መርየመ እና የሙሳ እህት መርየም ያለውን መመሳሰል ስንመለከት በይበልጥ ታሪኩን እንድንመረምር አድርጎናል። በዚህም ጉዳይ በርከት ያሉ ዳዒዎችና ለእስልምናና ለመሐመድ ዘብ(ጥበቃ) እቆማለሁ የሚሉት ዳዕዋጋንዲስቶች የሙግት ነጥብ ይሆኑናል ብለው የሚሰነዝሯቸውን ነጥቦች እንመልከት፦ የስም መመሳሰል፦ በዚህ የሙግት ነጥባቸው ላይ የኢሳ እናት የሆነችው የመረየም ወንድም ሃሩንና የሙሳ ወንድም ሃሩን ሁለት የተለያየ ማንነትና በተለያየ ጊዜ የነበሩ ሰዎች ናቸው ይላሉ። ይሄን የሙግት ነጥባቸውን ይደግፍልናል ብለው የሚጠቅሱት ሐዲስ አል-ሙጊራህ ኢብኑ ሹዕባ የሚባል ሰው ወደ ነጅራን በሄደ ጊዜ በዛ አካባቢ ያሉ ክርስቲያኖች በሱረቱል መርየምን (19:28) ላይ የተጠቀሰውን «…የሃሩን እኅት ሆይ!…» የሚልን ጽሑፍ እንዳነበቡና ሙሳ ደግሞ ከዒሣ ብዙ ጊዜ በፊት እንደነበር በነገሩት ጊዜ ጥያቄውን ይዞ ለመሀመድ አቀረበላቸው። መሀመድም በመልሳቸው “የድሮ ሰዎች ከራሳቸው በፊት ከነበሩት የነቢያቶች ስሞች ከነቢያቱ ህልፈት በኋላ ይጠቀሙ ነበር” ብሎ ነገረው(ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 38 ሐዲስ 13)። አስተውሉ፦ በሐዲሱ መሠረት የመጽሐፉ ባለቤቶች የሚባሉት ክርስቲያኖች ስለ ኢየሱስ እናት የማርያም ወንድም ስለሆነው አሮን የሚባል ወንድም እንዳላት በጭራሽ የማያውቁ እንደሆኑና አል-ሙጊራህ ኢብኑ ሹዕባ የሚባለው ሙስሊም ሙእሚን ግራ ተጋብቶ ጉዳዩ ጥያቄ እንደፈጠረበት እንመለከታለን። በተጨማሪም የምእመናን እናት የሆነችው አዒሻ (ኡም አል-ሙእሚኒን/أمّ المؤمنين‎) እንኳን እንደማታውቅ ከከዓብ (ረዐ) ጋር ባደረገችው ንግግር እንረዳለን[⁴] “…’የሃሩን(የአሮን) እህት!’ (የሱራ 19 28) የሙሴን ወንድም አሮንን አያመለክትም። ዓኢሻ(ረዐ) ለከዓብ(ረዐ) “ #ዋሽተሃል” በማለት መለሰችለት።….”(ተፍሲር ኢብን ከሲር 19:28) በእነዚህ ሁሉ ሰዎች ማለትም ለአንዳንድ ሙስሊሞች እንግዳ የሆነና በመሐመድ ዘመን የነበሩት የተማሩ ዐረብ ክርስቲያኖች(የመጽሐፉ ባለቤቶች) የማየታወቅን ታሪክ መሐመድ ከየት አምጥቶ ነው አሮን(ሃሩን) የሚባል የማርያም(መርየም ) ወንድም አለ ያለን? በተጨማሪም የኢሳ እናት የሆነችው የመረየም ወንድም ሃሩንና የሙሳ ወንድም ሃሩን የተለያዩ ሰዎች ናቸው ካሉን አንድ ወሳኝና አነጋጋሪ ጥያቄ መጠየቃችን አይቀሬ ነው በታሪክ ስለማይታወቀው ሰውዬ(የኢሳ እናት የመረየም ወንድም ሃሩን ተብዬው) እንደዚህ ያክል አስፈላጊና የኢሳ እናት መረየም በእርሱ እስከምትጠራ ስላስደረገው ሰው እንዴት ቁርአን ችላ ብሎ አለፈው እናም ስለሱ የሚናገሩ የታሪክ መዛግብት እንዴት ልናጣ ቻልን? ወይም ደግሞ የሙሴ (ሙሳ) ወንድም የሆነውን አሮንን(ሃሩን) የኢሳ እናት ለሆነችው ማርያም(መርየም) ወንድም መስሎት እንደነበር ይሄም ደግሞ የመሐመድ አላዋቂነት ማለትም በታሪክ ላይ የሰራው ወንጀል መሆኑን ማወቅ ይጠበቅብናል። ኢኽዋህ(إِخْوَة) የሙሳ ወንድም እና የመርየም ወንድም አንድ ማንነት ናቸው ስንል አማኞች ወንድም እና እህት ናቸው በሚል ቀመርና ስሌት ነው ይሉናል። ይሄም የሙግት ነጥባቸው መፍለክለኪያ(ማምለጫ) ያጣ ሰው ለማምለጫ ከሚፈጥረው ቀዳዳ ተለይቶ አልታየኝ። በሃገሬው አባባል “…ከቀዳዳ ይሻላል ጨምዳዳ…” እንደሚባለው ነጥቦቻቸው የመሐመድን ስህተት መደበቅ ሳይችልላቸው ሲቀር ከአንዱ ወደ አንዱ በይሻላል መንፈስ ይራወጣሉ። ለማንኛውም በአማኞች መካከል ኢኽዋህ(إِخْوَة) ማለትም ወንድማማችነትና እህትማማችነት ቢኖርም አሁንም የሱረቱል መርየም(19:28) ከጥያቄ አያመልጥም። ቁርአኑ ስለ ሙሳ ከወንድሙ ሃሩን ይልቅ በስፋት ነግሮን ሳለ ሙሳ ሳይጠቀስ ሃሩን የተጠቀሰበት አግባብ ግልጽ አይደለም።ደግሞስ መርየም አባቷ ኢምራን እያለ በሙሳ ወንድም በሃሩን ስም መጠራቷ ምንን ያመለክታል? ደግሞም በሌላ ክፍል በሱራ 33 እና 66:12 ላይ “የኢምራን ሴት ልጅ” በመባሏ ወደ ሱራ 19:28 ስንመጣ ከሩቅ ዘመን ባለ ሰው ስም መጠራቷ ጉዳዩን የበለጠ ብዥታንና እና ችግርን አስከትሏል። ለዚህ ሁሉ ጥያቄ መልስ የሚሆነው የመሐመድን ስህተት መቀበል ነው። በተጨማሪም መሐመድን ለዚህ ትልቅ ስህተት ያበቃው አንዳንድ ምንጫቸው በቅጡ ከማይታወቁ በክርስትናው ላይና በአይሁዳውያን መጽሐፍት ላይ ከሚጨመሩ አፈታሪኮች የሰማውን በራሱ አገላለጽ ስለሚዘግብ ነው። ሱረቱ መርየም የተወሰኑ ክፍሎች የአፖክሪፋን ታሪኮች እንደ የያዕቆብ ፕሮቶቫንጄሊየም (Protoevangelium of James) እና የሐሰተኛው-ማቴዎስ ወንጌል(gospel of Pseudo-Matthew) ካሉ አፈ ታሪኮች የአዋልድ ታሪኮች ተመሳሳይነት ያለው ታሪክ እናገኝበታለን። ለምሳሌ የቴምር ዛፉ ስር የተፈጠረው ታሪክ[⁵] ስለ መርየም ወላጆች ታሪክ[⁶] ለአብነት ተጠቃሽ ናቸው። በተጨማሪም በአረባዊቷ ምድር በፍልስጤም ውስጥ በቅድስት ድንግል ማርያም የተሰየመ የባይዛንታይን ቤተክርስቲያን አለ። ይህ ቤተክርስቲያን ከእስልምና ወግ ጋር ጥልቅ እና የተወሳሰበ ግንኙነት አለው እንዳለው ታሪክ ይነግረናል። በመሐመድ ዘመን አካባቢ ይህች ቤተክርስቲያን የክርስትና አምልኮ ማዕከል ነበረች። በቅዳሴ ወቅት ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ከሚነበበው ከካቶሊክ እና ከኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በተቃራኒ በዚህ ጊዜ ለንባብ ከአፖክሪፋ እና ከሌሎች ቀኖናዊ ያልሆኑ መጽሐፍት መነበቡ የተለመደ ነው። በተጨማሪም የተለያዩ የክብረ በዓላት የምታከብር ቤተ ክርስቲያን ነበረች። ለምሳሌ ላይ በነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ቀን 14 ከነብዩ ኤርምያስ ሕይወትም ከአዋልድ መጽሐፍት ይነበብ ነበር። በምንባቡ ላይ መሐመድ በሱረቱል በመርየም ላይ እንዳሰፈረው አይነት ማለትም ሃሩን(አሮን) የማርያም (መርየም) ወንድም በማለት የተጠቀሰን ጽሑፍ እናገኛለን[⁷]፦ “ነቢዩ [ኤርምያስም] እንዲህ አለ – መምጣቱ ለእርስዎ እና ለሌሎች ልጆች በዓለም ምልክት መጨረሻ ይሆናል ።57 እንዲሁም የተደበቀውን ታቦት ከዓለት ላይ የሚያወጣ የለም ከማርያም ወንድም አሮን በስተቀር ።(The Lection of Jeremiah) በተመሳሳይ ሁኔታ ቁርአኑ ስለ ማርያም (መርየም) ሲናገር ሃሩን(አሮን) የማርያም (መርየም) ወንድም እንደሆነ ዘግቦልን አግኝተናል፦ 19፥28 « የሃሩን እኅት ሆይ! አባትሽ መጥፎ ሰው አልነበረም፡፡ እናትሽም አመንዝራ አልነበረችም» አሏት፡፡ يَا أُخْتَ هَارُونَ مَا كَانَ أَبُوكِ امْرَأَ سَوْءٍ وَمَا كَانَتْ أُمُّكِ بَغِيًّا በመጨረሻም ለመሐመድ ዘብ እንቆማለን ባዮቹ አብዱሎች ታሪክን በመደበቅ የመሐመድን ስህተቶችና አላዋቂነቱን ለመደበቅ መፍጨርጨራቸው የሚያዋጣ አይደለም። መሐመድ ከታሪክ አንጻር ሲሳሳት ይሄ የመጀመሪያው እንዳልሆነ ከታሪክ መዛግብት ዘንድ ብዙ መረጃዎችን ስንበረብር የሚጋለጥ ሐቅ ነው። እስከምንገናኝ በክርስቶስ ፍቅር ቸር ሰንብቱ! ማጣቀሻዎች እና ማስፈንጠሪያዎች [¹] https://al-maktaba.org/book/9783/383 [²] የተለያዩ የታሪክ ተመራማሪዎች እና ጸሐፊዎች ስለ ሙሴ የውልደት ዘመን ላይ የተለያየ አስተያየቶችን ሰንዝረዋል። በአማካይ ከወሰድነው ሙሴ እና ወንድሙ አሮን የተወለዱት 1400-1500  ዓ.ዓ ገደማ እንደሆነ አብዛኞቹ ምሁራን ይስማሙበታል(Seder Olam Rabbah,Jerome’s Chronicon (4th century) gives 1592 for the birth of Moses,The 17th-century Ussher chronologycalculates 1571 BC (Annals of the World, 1658 paragraph 164) [³] The gospel of the birth of Mary, 1:1-2, Gambero, Luigi (1999). Mary and the Fathers of the Church: The Blessed Virgin Mary in Patristic Thought. Ignatius Press.ISBN 978-0-89870-686-4. [⁴] https://quran.al-islam.com/Page.aspx?pageid=221&BookID=11&Page=1 [⁵] The Gospel of Pseudo-Matthew Chapter 20 [⁶] Protoevangelium of James Gospel

ማርያም የሐሩን እህት? Read More »

የመስዋዕቱ ልጅ ኢስሐቅ ወይስ ኢስማኢል?

ኢድ አል አድሃ(عيد الأضحى) ኢድ(عيد) ማለት በአል፣ ድግስ ወይም ለመታሰቢያነት የሚከበር ነገር ማለት ሲሆን አድሃ (أضحى) ወይም ቁርበን (قربان) ወይም ደግሞ የእብራይስጡ አቻ ቃል ቆርባን(קׇרְבָּן) ማለት “መስዋዕት/መባ” ማለት ነው። ኢድ አል አድሃ ሁለተኛው የሙስሊም ወገኖቻችን ክብረ በአል ነው። በዚህም ክብረ በአል ሙስሊም ወገኖቻችን ለመስዋዕትነት የሚሆነውን የበግ፣ የግመል፣ የፍየል ወየም የጠቦትን…ወዘተ የመሳሰሉትን የእንስሳትን ደምን ያፈሳሉ። የበአሉ እርሾ ወይም ጅማሮ በቁርአን ውስጥ የኢብራሂም(ዐሰ) ልጁን ለአምላኩ ለመሰዋት የታዘዘበትን ቀን ለማሰብ ሲባል የሚከበር በአል ነው። በቁርአን ላይ አላህ በሱረቱ አልሷፍፋት (የተሰላፊዎቹ ምዕራፍ) ላይ ስለ ተሰላፊዎች እምነት በሚናገርበት ክፍል በቁጥር 83 ላይ ከአማኞች መካከል የሆነው ኢብራሂም (ዐሰ) አንደኛው እንደሆነ ይናገራል። በዛው ክፍል በቁጥር 100 ላይ ደግሞ ኢብራሂም (ዐሰ) አንድን ጸሎትን ሲጸልይ እንመለከታለን፦ As-Saffat 37:100ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡(رَبِّ هَبْ لِى مِنَ ٱلصَّلِحِينَ) የኢብራሂምም አምላክም ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም ባሪያውን አበሰረው። ኢብራሂም (ዐሰ) ከባዱ ፈተና የሚጀምረው በቁጥር 102 ላይ ነው። አምላኩ የሰጠው ልጅ ለስራ በደረሰ ጊዜ ኢብራሂም (ዐሰ) በራዕይ አንድ ልጁን እንደሚያርድ ሁኖ ያልማል። እርሱም ለልጁ ስለ ራዕዩ ምን እንደሚያስብ በጠየቀው ጊዜ “የታዘዝከውን ሥራ” ብሎ ሲፈቅድለት እንመለከታለን። አሁን ዋናው ጉዳይና ጥያቄ ያ ለኢብራሂም (ዐሰ) የተበሰረው የመስዋዕቱ ልጅ ማነው? የሚለው ንግርት ነው! የዘመናችን የሙስሊም ኡስታዞች ሽንጣቸውን ገትረው በመከራከር በቁርአኑ ላይ የመስዋዕቱ ልጅ ኢስማኢል  ለማስመሰል የቁርአኑን አያህ የማይቀባቡት ነገር የለም። ከሁሉም በላይ ደግሞ አጃኢብ የሚያስብለው ጥርት እና ጥንፍፍ ብሎ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተነገረለትን የቃል ኪዳን ልጅ ይስሐቅን በእስማኤል ተክተውና አንሻፈው የመስዋዕቱ ልጅ እስማኤል እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል ማለታቸው ነው። “..የያዙት ነገር..” እንደሚሉት አበው በእኛ ዘንድ የሙስሊም ኡስታዞች መካከል ይሄንን ዜማ መስማቱ የተለመደ ነው። ሲጀመር ኡስታዞቹ የማይሆን የማይሆን የሙግት ነጥቦቻቸውን እየሰካኩ ለሙስሊሙ ተደራሲያን እየፈተፈቱ ሲያጎርሷቸው እኛንም (የክርስቲያኑን ማህበረሰብ) ለማታለል መጣጣራቸው ሳስብ ይገርመኛል። ለማንኛውም የኡስታዞቻቸውን ድርሳነ ባልቴት ወይም የአሮጊቶች ተረት የሆነውን የሙግት ሐሳባትን በሁለት ጎራዎች ከፍለን ስለ መስዋዕቱ ልጅ ማንነት እንመለከታለን፦ የቁርአናዊ ሙግት በመጀመሪያ ኢስማኢል ነብይ መሆኑ ለመስዋዕትነት የተዘጋጀው ልጅ እርሱ ነው የሚያስብለን አንድምታ የለም። ምክንያቱም እንዲሁ ኢስሐቅም ነብይ መሆኑን ቁርአናቸው ይነግረናል(Al-‘Ankabut 29:27)።[1] ስለዚህ ስለ ኢስማኢል ነብይነት መጥቀስና ማጠቃቀስ ጉንጭ ማልፋት ካልሆነ በስተቀር ለሙግቱ እንብዛም ውጤት የለውም። ለማንኛውም ኡስታዞቹ ያነሷቸውን ዋና ዋና ነጥቦችን እንመለከታቸዋለን። ቀጠሮ አክባሪው የዘመናችን የሙስሊም አቃብያነ እምነት ነን የሚሉት በሱረቱ መርየም 54 ላይ የተጠቀሰውን ክፍል ከሱረቱ አልሷፍፋት 102 ጋር በማጣመር የተሳሳተ ምስስሎሽን (wrong analogy) በመፍጠር ለመስዋዕትነት የቀረበው ኢስማኢል መሆኑን ለማሳየት ሞክረዋል። ነገር ግን በክፍሉ ላይ አውዳዊ ምልከታ ስናደርግ ሙግታቸው የሚያስኬድ ሁኖ አናገኘውም፦ Maryam 19:54በመጽሐፉ ኢስማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ መልክተኛ ነቢይም ነበር፡፡(وَٱذْكُرْ فِى ٱلْكِتَٰبِ إِسْمَٰعِيلَۚ إِنَّهُۥ كَانَ صَادِقَ ٱلْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا ) በዚህ ክፍል ላይ አላህ የኢብራሂምን ልጅ ኢስማኢልን ሲያመሰግነው እንመለከታለን። ኢስማኢል የአረቦች ሁሉ አባት ነበር። በተጨማሪም እርሱ ለቃለ ማሐላው እውነተኛና ታማኝ እንደነበር የሙስሊም ሊቃውንት ይናገራሉ።[2] የክፍሉን አውደ ሕታቴ ለመረዳት ቁጥር 55ን መመልከቱ አስፈላጊ ነው፦ Maryam 19:55ቤተሰቦቹንም በሶላትና በዘካ ያዝ ነበር፡፡ እጌታውም ዘንድ ተወዳጅ ነበር፡፡(وَكَانَ يَأْمُرُ أَهْلَهُۥ بِٱلصَّلَوٰةِ وَٱلزَّكَوٰةِ وَكَانَ عِندَ رَبِّهِۦ مَرْضِيًّا ) ኢስማኢል በጌታው ዘንድ ተወዳጅ የሆነበትና ከላይ ደግሞ አላህ ኢስማኢልን እንዲያስቡ ለምእመናን ሲናገር በኢስማኢል የግብር ጉዳይ ረገድ መሆኑ ግልጽ ነው። ኢስማኢል ለአላህ ለሆኑ ስራዎች ላይ ታማኝና አክባሪ ነብይ መሆኑን ከክፍሉ አውድ መረዳት እንችላለን። እንደውም የእንግሊዘኛው ትርጉም ቁጥር 54ን የሚገልጸው “he was true to his promise” ለቃለ መሐላው እውነተኛ ወይም ታማኝ እንደሆነ በሚያሳይ መልኩ ነው። And mention in the Book, Ishmael. Indeed, he was true to his promise, and he was a messenger and a prophet./English – Sahih International (Maryam 19:54)/ በተጨማሪም ኢብን ጁረይጅ ስለ ኢስማኢል ሲናገሩ፦ “He did not make any promise to his Lord, except that he fulfilled it./የሚፈጽመውን ካልሆነ በቀር ኢስማኢል ምንም አይነት ቃለ መሐላ ለጌታው አይገባም “Ibn Jurayj ስለዚህ ኢስማኢል ለቃለ መሐላው እውነተኛ፣ ታማኝና አክባሪ መሆኑን የሱረቱ መርየም ቁጥር 54 አውዳዊ አንድምታው ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ቀጠሮ ከሚለው ፍታቴ ይልቅ ቃለ መሐላ ወይም ቃልኪዳን(promise) እንደሆነ የክፍሉ ዙሪያ ገባ ይነግረናል። “ቀጠሮውን አክባሪ” የሚለው ኃይለቃል በተጨማሪም የማያስኬደው በመጀመሪያ አላህ በሱረቱ አልሷፍፋት 102 ላይ ራዕይን ያሳየው ለኢብራሂም (ዐሰ) እንጂ ለልጆቹ ለኢስሐቅ ወይም ለኢስማኢል ፈጽሞ አይደለም። فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعْىَ قَالَ يَٰبُنَىَّ إِنِّىٓ أَرَىٰ فِى ٱلْمَنَامِ أَنِّىٓ أَذْبَحُكَ فَٱنظُرْ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰأَبَتِ ٱفْعَلْ مَا تُؤْمَرُۖ سَتَجِدُنِىٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّبِرِينَ ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡ በተጨማሪም አላህ የመስዋዕቱን ቀጠሮ የሰጠው ለአባቱ ለኢብራሒም(ዐሰ) እንጂ ለልጁ አልነበረም። ምክንያቱም የራዕዩና የትእዛዙ አክባሪ አባቱ እንጂ ልጁ አይደለም። በተጨማሪም በቀጠሮው ቀን ለመሰዋት ልጁን የወሰደው አባትየው እንጂ ልጁ አይደለም። ስለዚህ ለመስዋዕትነት የተቀጠረው ኢስማኢል የቀጠሮው አክባሪ ነበር የሚለው አንድምታ ኪስ ወለድ እንጂ አውዳዊ አለመሆኑን ለመረዳት አያዳግትም። የኢብራሒም ጸሎት ሌላው የሙግት ነጥብ ብለው የሚያቀርቡት ደግሞ “ኢስማኢል/إِسْمَٰعِيْل”  ማለት “አምላክ ይሰማል” ማለት ስለሆነ ኢብራሒም ደግሞ በቁጥር 100 ላይ ወደ አላህ በጸለየው መሰረት ልጅን ሰጠው የሚል ነበር። ነገር ግን ከአውዱ ተነስተን ስንመለከት አላህ ለኢብራሒም በጸሎቱ መሰረት የተሰጠው ልጅ ኢስሐቅ እንጂ ኢስማኢል እንዳልሆነ እንረዳለን። ሲጀመር ኢስሐቅ(إسحاق) ወይም በእብራይስጥ ይሽሐቅ(יִשְׂחָק) ደስታ፣ ሳቅ ወይም ብስራት ማለት ነው። በቁጥር 100 ላይ ነብዩ ኢብራሂም(ዐሰ) ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ(رَبِّ هَبْ لِى مِنَ ٱلصَّلِحِينَ) ብሎ ከጸለየ በኋላ፤ በቁጥር 101 ላይ ጌታውም ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው (فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍ) ብሎ ሲናገር እንመለከታለን። አስተውሉ! የጌታው መልስ ላይ “አበሰርነው” የሚለውን ቃል ከኢስሐቅ ጋር እንጂ ከኢስማኢል የስም ትርጉም ጋር ፈጽሞ የሚገናኝ አይደለም። እንደውም ስለ ልጁ ማንነት በዛው ሱራ በቁጥር 112 ላይ ግልጽ አድርጎ የብስራቱ ልጅ ኢስሐቅ እንደሆነ ይነግረናል በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን(وَبَشَّرْنَٰهُ بِإِسْحَٰقَ نَبِيًّا مِّنَ ٱلصَّلِحِينَ)በተጨማሪ በሱረቱ ሁድ 11፡69-71 ያለውን ክፍል ስንመለከት በቁጥር 101 ላይ ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው የሚለው ንግግር ለኢስሐቅ መሆኑን ግልጽ የሚያደርግ ክፍል ነው። 11:69 – መልክተኞቻችንም ኢብራሂምን በ(ልጅ) ብስራት በእርግጥ መጡት፡፡ ሰላም አሉት፡፡ ሰላም አላቸው፡፡ ጥቂትም ሳይቆይ ወዲያውኑ የተጠበሰን የወይፈን ስጋ አመጣ፡፡11:70 – እጆቻቸውም ወደ እርሱ የማይደርሱ መኾነቸውን ባየ ጊዜ ሸሻቸው፡፡ ከነሱም ፍርሃት ተሰማው፡፡ «አትፍራ እኛ ወደ ሉጥ ሕዝቦች ተልከናልና» አሉት፡፡11:71 – ሚስቱም የቆመች ስትኾን (አትፍራ አሉት) ሳቀችም፡፡ በኢስሐቅም አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ (በልጁ) በያዕቁብ (አበሰርናት)፡፡ ከኢስሐቅ ሌላ አካል በዚህኛው የሙግት ሐሳብ ላይ ደግሞበቁጥር 112 በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን በሚለው ክፍል ላይ በኢስሐቅም ስለሚል “-ም” የምትለው ጥገኛ ምእላድ ከኢስሐቅ ተጨማሪ ሌላ አካል እንዳለ ያመለክታል የሚል ሙግት ነው። ነገር ግን ይሄ ሐሳብ ፈጽሞ የሚያስኬድ አይደለም። አብዱሉ በክፍሉ ላይ ሁለት ልጅ የተባሉ አካላት እንዳሉ ይናገራል። የመጀመሪያው ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም ሲሆን ሁለተኛው በኢሥሐቅ ብሎ ከፋፍሎ እንመለከታለን። እንደዛ ከሆነ የሙግቱ ሃሳብ አጠያያቂ ይሆናል። ምክንያቱም በእርሱ ሎጂክ ከሄድን በቁጥር 101 ላይ አላህ ለኢብራሒም ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው (فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍ ) በሚለው አንቀጽ ላይ ወጣት ልጅም በሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት “-ም” የምትለው ምእላድ አሁንም በእነርሱ ሎጂክ ኢስማኢል ነው ብለው ከሚያምኑት አካል ሌላ ከእርሱ

የመስዋዕቱ ልጅ ኢስሐቅ ወይስ ኢስማኢል? Read More »

መሬትን ተሸካሚው ፍጡር  (“አል-ኑን/النون”)

በእስልምናው አስተምህሮት ውስጥ አፈታሪካዊ እና ተረታዊ ከሆኑት ታሪኮች መካከል አንደኛው ግዙፉ እስላማዊው አሳ ነባሪ ( الحوت الإسلامي ፣ አል-ሁት አል-ኢስላሚ) ይሄም ፍጡር ምድርን በጀርባው እንደሚሸከም የተገለጸለት  አፈታሪካዊው ፍጡር ነው፡፡ ታዳ  ይሄ እስላማዊው አውሬ/አሳነባሪ(አል-ሁት/ٱلْحُوتِ) በቁርአን ላይ “ምድር ተሸካሚ አሳ” ወይም “አል-ኑን/النون” ተብሎ ተጠርቷል። ቁርአኑ ስለዚህ ፍጡር ግልጽ በሆነ ሁኔታ አላስቀመጠልንም። በዚህም ምክንያት በአንዳንድ የሙስሊም ሊቃውንቶች መካከል እስካሁኑ ሰአት ድረስ ያልተፈታ ትልቅ ንትርክን የፈጠረ ለዘመናዊው ሳይንስ ጥናቶች እንግዳና አጠያያቂ የሆነ ጉዳይ ነው። እኔም ስለዚህ ፍጡር ጉዳይ በስፋት በመመልከት አንዳንድ እስላማዊ ጽሁፎችን ማለትም ሐዲሳትን እና የተለዩ ተፍሲራትን እያገላበጥን ለማሳየት ቀርቤያለሁ። ➙ ከላይ በጨረፍታ ለመመልከት እደሞከርነው “አል-ኑን/النون” በውሀ ውስጥ ከሚኖሩ የአሳ ዝርያዎች መካከል አንዱ ነው። በቁርአን በሱረቱል አል-ቀለመ በአንደኛው አያት ላይ ተጠቅሶ እናገኘዋለን። ይሄንን አያት በእስልምናው ማህበረሰብ ውስጥ እጅጉን እውቅና ካላቸው የቁርአን ተፍሲሮች (ኢብን-ከሲር፣ አል-ቁርጡቢ፣ ጃለለይን እና አት-ጠበሪ) እንደሚያስረዱን ከሆነ “ኑን” የሚባለው ግዙፍ አሳ ነባሪ እንደሆነና ምድርን የተሸከመ ፍጡር እንደሆነ ይነግሩናል። አል-ቀለም 68:1نٓۚ وَٱلْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَነ.( #ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡ ኢብን ከሲር አል-ቀለም 68:1 ተፍሲር፦ታላቁ ሙፈሲር ኢብን ከሲር በተፍሲሩ ላይ ስለ ኑን ሲናገር፦ አላህ ‹ ኑን› የተባለውን ከፈጠረ በኋላ ምድር በኑን ጀርባ ላይ እንደዘረጋ ይናገራል፡፡ ከዛም ተረቱ ይቀጥላል #ኑን የሚባለው ፍጡር ደነበረ ወይም ተረበሸ ይለናል። በዚህ መሀል ምድር ማረግረግ ወይም መንቀጥቀጥ ጀመረች። አላህ ለዚህ ችግር ሲል ተራሮችን ፈጠረ። እነዚህም ተራሮች ምድር እንዳትነቃነቅ እንደ ችካል ቸከላቸው ይለናል። እንደውም በቁርአን 78:7 ላይ “…ጋራዎችንም(ተራሮችን) ችካሎች አላደረግንምን(وَٱلۡجِبَالَ أَوۡتَادًا)?)…”  አላህ ተራሮችን የቸከላቸው የመሬትን መንቀጥቀጥ ለማስተካከል እንደሆነ ተፍሲራት ይነግሩናል(ጃላለይን, ኢብን ከሲር ተፍሲር)። ምን ይሄ ብቻ አሁም አፈታሪካዊ ተረቱ አላበቃም አል ባግሃዊ እና ሌሎች የሙስሊም ሙህራኖች እንደተናገሩት በዚህ ዓሣ ጀርባ ላይ ውፍረቱ ከሰማይና ከምድር የሚበልጥ ትልቅ ዓለት አለ፡፡ ከዚህ ዓለት በላይ ደግሞ አርባ ሺህ ቀንዶች ያሉት ኮርማ ቆሟል፡፡ በዚህ ኮርማ ላይ ሰባቱ መሬቶችና በውስጣቸው የሚገኙት ሁሉ ተቀምጠዋል ብለው ያስባሉ። እስቲ ይሄን ታሪክ ከኢማም ኢብን ከሲር ተፍሲር በተወሰነ መልኩ እንመልከት፦ “…ከዚያም አላህ ‹ኑን› የተባለውን ከፈጠረ በኋላ ሰማይ የተፈጠረበት ጭስ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ከዚያም ምድር በኑን ጀርባ ላይ ተዘረጋች፡፡ ከዚያም ኑን ስለደነበረ ምድር ማረግረግ ጀመረች፤ ነገር ግን (አላህ) ምድርን እንዳትንቀሳቀስ አድርጎ በተራሮች ቸከላት… “ኢብን አቡ ኑጃኢህ እንደተናገረው ኢብን አቡ በኪር በሙጃሂድ እንዲህ ተብሎ ተነግሮት ነበር፣ “ኑን ከሰባቱ መሬቶች በታች የሚገኝ ታላቁ አሣ እንደሆነ ይነገራል፡፡” በተጨማሪም አል ባግሃዊ (አላህ ነፍሱን ያሳርፋትና) እንዲሁም ሌሎች ሐታቾች እንደተናገሩት በዚህ ዓሣ ጀርባ ላይ ውፍረቱ ከሰማይና ከምድር የሚበልጥ ትልቅ ዓለት አለ፡፡ ከዚህ ዓለት በላይ ደግሞ አርባ ሺህ ቀንዶች ያሉት ኮርማ ቆሟል፡፡ በዚህ ኮርማ ላይ ሰባቱ መሬቶችና በውስጣቸው የሚገኙት ሁሉ ተቀምጠዋል፡፡…”[1] ኑን ለሚለው ቃል ትርጓሜ ሲያስቀምጥ ደግሞ “…ኑን የሚባለው ትልቅ አሳነባሪ ነው(Nun is a big whale/نۤ حوت عظيم)…” በማለት ኢብን ከሲር ትንታኔውን አስቀምጧል።[2] አል-ቁርጡቢ ተፍሲር 68:1 نۤ> الحوت الذي تحت الأرض السابعة>”…<ኑን>ከሰባተኛው(السابعة) መሬት(الأرض) በታች(تحت) የሚገኘው አሳ ነባሪ(الحوت) ነው….”[3] በአል-ቁርጡቢ ተፍሲር መሰረት ” ኑን” የሚባለው ከሰባተኛው  መሬት በታች የሚገኝ አሳ ነባሪ እንደሆነ ይነግረናል። ልብ በሉ “…ከሰባተኛው(السابعة)…” ሰባት ምድር እንዳለም ከላይ በኢብን ከሲር ተፍሲር ላይ ተመልክተናል። እነርሱም ተደራራቢ እንደሆኑ “ታሐት(تحت)” ወይም “ከታች/ከስር” የሚለው ቃል ያስረዳናል። ተፍሲር አት-ጠበሪ 68:1አት-ጠበሪ በሱረቱል አል-ቀለም 68:1 ላይ ማብራሪያ ሲያስቀምጥ እንዲህ ብሏል፦“…هو الحوت الذي عليه الأرَضُون…”“…ሰባቱ ምድሮች የተቀመጡበት ፍጡር አሳ ነባሪ(الحوت) ነው…”[4] በእስልምናው ኮስሞሎጂ መሰረት አላህ ሰባት ሰማያትን እንደፈጠረ ሁሉ ሰባት ምድሮችንም ፈጥሯል(Quran 65:12)። እነዚህም ጠፍጣፋ ምድሮች በአሳ ነባሪው ላይ ተደራርበው ተቀምጠው እንደሚገኙ ጥንታዊ የሙስሊም ሊቃውቶች ይነግሩናል። ተፍሲር አል-ከቢር(አር-ረዚ)/tefsir Al kabir(by Ar-Razi)፦ “…بالحوت الذي على ظهره الأرض وهو في بحر تحت الأرض السفلى…” በዚህም ተፍሲር ላይ በጀርባው ምድር የሚሸከመው ዓሳ ነባሪ እንደሆነና አል-ከቢር እዚህ ዓሳ ነባሪ ጀርባ ላይ ሚዛናዊ የሆኑ ጠፍጣፋ መሬቶች እንዳሉ  ይነግረናል፡፡[5] ተፍሲር አል-ቃዲር/Tafsir Al-Qadir (by Shawkani) ተፍሲር አል-ቃዲር/Tafsir Al-Qadir (by Shawkani) ይህ ተፍሲር ከ 18 ኛው ክፍለዘመን ጀምሮ ዓለም ዓሳ ነባሪ ጀርባ ላይ ተሸክሟል የሚል ሀሳብን በመደገፍ ያረጋግጣል። “….ምድርን የተሸከመው ፍጡር አሳ ነባሪ/الحوت ነው…..”/Fath Al-Qadir on 68:1__[6] ሐዲስ ከኢብን አባስ (ቱርጁማን ኡል-ቁርአን/ترجمان القرآن)(ሐዲስ ከአት-ጠበሪ) ኢብን አባስ እንደተናገረው፦አላህ የፈጠረው የመጀመሪያ ነገር ብእርን  ስለነበረ “ጻፍ!” አለው፡፡ እናም እስከ ሰዓቱ (የፍርድ ቀን) ድረስ ምን እንደሚሆን ጽፏል፤ ከዚያም ኑንን ከውሃ በላይ ፈጠረ ከዚያም ምድርን በእርሱም ላይ ተጫነች፡፡(ታሪኽ አት-ታባሪ) [7] ይህም ሀዲስ(ትረካ) በሀዲሳት ሰንሰለት  ትክክለኛ(ሰሒህ/صحيح) ትረካ ተደርጎ ተቆጥሯል፡፡[7] መሐመድ ለኢብን አባስ ዱዓ (ጸሎት) ስላደረገ አላህም የቁርአንን ትክክለኛ አተረጓጎም ያስተምረው ነበር፡፡እንዲሁም ኢብን አባስ (ቱርጁማን ኡል-ቁርአን/ترجمان القرآن) “የቁርአን ተርጓሚ” ተብሎ ተጠርቷል ፣ ምክንያቱም ስለ ራእዮች ትርጓሜ (ቃል በቃል መተርጎም) የሚሰጥና ጥልቅ ዕውቀት ያለው ሰው ነበር። ኢብኑ ዐባስ (ራአ) እንደተናገሩት፦ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) አቅፈውኝ “አሏህ ሆይ! የመጽሐፉን (ቁርአን) እውቀት አስተምሩት ፡፡ ”(ሳሂህ ቡኻሪ 9:92:375) ታድያ ይህ በቁርአን ጥልቅ እውቀት ያለው አሊም ተራራዎቹ በቁርአን ውስጥ እንደ ችካል እንዴት እንደተደረጉ የእርሱ ትረካ ያስረዳል፡፡ ምክንያቱም በባህላዊው እስላማዊ የኮስሞሎጂ መሠረት ምድር ከዓሣ ነባሪው ጀርባ ላይ ትነቃነቅ (ትንቀጠቀጥ) ስለነበረ አላህ ምድርን ዓሣ ነባሪው ላይ ተረጋግታ እንድትቀመጥ ተራሮችን እንደ ችካል እንዳደረጋቸው በግልጽ ሁኔታ ተርኮልናል፡፡ በመጨረሻም ከዚህ ሁሉ መረጃዎችና ማስረጃዎች የምንረዳው ነገር ቢኖር አላህ ሰባት መሬቶችን ፈጥሮ በአሳ ነባሪው(“አል-ኑን/النون” ) ጀርባ ላይ ደራረቦ በማስቀመጥ ከዛም አሳ ነባሪው(“አል-ኑን/النون” ) ሲደነብር መሬት እዳትነቃነቅ በተራሮች በመቸከል እንድትረጋጋ አድርጓል። ይባስ ብሎም በዚህ ዓሣ ጀርባ ላይ ውፍረቱ ከሰማይና ከምድር የሚበልጥ ትልቅ ዓለት አለ፡፡ ከዚህ ዓለት በላይ ደግሞ አርባ ሺህ ቀንዶች ያሉት ኮርማ ቆሟል፡፡ በዚህ ኮርማ ላይ ሰባቱ መሬቶችና በውስጣቸው የሚገኙት ሁሉ ተቀምጠዋል ብለው በማሰብ ይህ ለሳይንስና ለእውነታ ሆድና ጀርባ የሆነን ነገር ከአንዳንድ የመሰለኝን ልናደርግ ከሚሉ ፈላስፋዎች ቀጥታም ሆነ ተጨማምሮበት የተቀዳ አፈታሪክን የአምላክ መገለጥ ነው ብሎ መቀበል በጣም ሞኝነት ነው። አንዳንድ የዘመኔ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ስኮላሮችና ዳኢዎች ይሄ ነገር አልዋጥ ሲላቸው የውሸት የትረካ ሰነድ ወይም አምላካዊ ንግግር የሆነ ሀሳብ አይደለም ይሉናል።[8] ነገር ግን አይኑ የፈጠጠ በድሮ ዘመን በነበሩት የእስልምና ሊቃውንቶች መካከል ተቀባይነትን ያተረፈ ታሪክ እንደሆነ ከተፍሲራትና ከሐዲስ ለመመልከት ችለናል። ይሄን የመሰለ ተረትና አፈታሪክ ታቅፈው ነው እነ ዶክተር ዛኪር ናይክና ቢጤዎቹ ቁርአን ከሳይንስ ጋር አይጣረስም የሚሉን። በመሰናበቻዬም አንድ ነገር ተናግሬ ልደምድም፦ እውነት ቁርአን የፈጣሪ ንግግር ነውን? ከሆነስ ለምን ከሐቅና ከሳይንስ ጋር ላይስማማ ሊጣረስ ቻለ? እውነትን ፈልጉ እውነትም አርነት ያወጣችኋል። ማጣቀሻዎችና ማስፈንጠሪያዎች [1] Tafseer Ibn Katheer;Online Edition: http://quran.al-islam.com/Tafseer/DispTafsser.asp?l=arb&taf=KATHEER&nType=1&nSora=68&nAya=1 [2] https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=0&tTafsirNo=7&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [3] https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=1&tTafsirNo=5&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [4]  https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=1&tTafsirNo=1&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [5]  https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=1&tTafsirNo=4&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [6] https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=1&tTafsirNo=9&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [7]  https://hdith.com/?s=%D8%AB%D9%85+%D8%AE%D9%84%D9%82+%D8%A7%D9%84%D9%86%D9%88%D9%86+%D9%81%D9%88%D9%82+%D8%A7%D9%84%D9%85%D8%A7%D8%A1%D8%8C+%D8%AB%D9%85+%D9%83%D8%A8%D8%B3+%D8%A7%D9%84%D8%A3%D8%B1%D8%B6+%D8%B9%D9%84%D9%8A%D9%87 [8]  https://islamqa.info/en/114861

መሬትን ተሸካሚው ፍጡር  (“አል-ኑን/النون”) Read More »

የቀድሞ ነብያት ክርስቲያን አልነበሩምን?

ለሙስሊም ሰባኪያን ሙግት ምላሽ የእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ የተገለጠ አምላክ መሆኑንና ከእርሱም በፊት የነበሩት ነብያት እና የእምነት አባቶች ከዛም በመቀጠል በሐዲስ ኪዳን የነበሩት ሐዋርያቶች እርሱን እንደተከተሉ የክርስትና መሠረት እምነት የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል። በተጻራሪው ግን ቅዱሳት መጻሕፍት ተጽፈው ከተጠናቀቁ ከብዙ መቶ ዓመታት በኋላ የመጣው እስልምና ደግሞ በቀድሞ ነቢያት ተወርቶ እና ተሰብኮ የማይታወቅ አምላክ አስተዋወቀን፤ ከዛም አልፎ ተርፎ ተከታዮቹ ሙስሊም እንጂ ክርስቲያን አይደሉም ብሎ ብቻውን ቆሞ ያስተምራል። ኢስላም ናቸው እንጂ ክርስቲያን አይደሉም የሚለው ንግግር በብዙ ሙስሊሞች ዘንድ እንደ ትልቅ ርዕስ አድርገው ክርስቲያኖችን ጋርም በጥያቄ መልክ ሲቀርብ ይስተዋላል። እኛም ይህን አስተምሮታቸው ከሆነው ከቁርኣን የመነጨ እና ጥያቄያቸው በራሱ ማስረጃ የሌለው ኪስ ወለድ ሙግት ሀሳብ መሆኑን እንመለከታለን። በመጀመሪያ ግን ክርስቲያን እና ደቀመዛሙርት ማለት ምን ማለት ነው? ክርስቲያን(Χριστιανούς/ክሪስትያኑስ)፦ ማለትም የክርስቶስ ተከታይ ወይም በክርስቶስ ህግ እና ትምህርት የሚመራ ማለት ነው። የእርሱ አቻ ቃል የክርስቶስ ደቀመዝሙር/μαθητής  ሲሆን ጥቅልል ትርጉሙ “ የክርስቶስ ተማሪ ”ወይም” የክርስቶስ ተከታይ” ማለት ነው። የሐዋርያቶች ደቀመዝሙር የነበሩት ከማን እግር ስር እንደተማሩ ለመግለፅ ይህንን ቃል ይጠቀሙትም ነበር። ለቅምሻ ታህል ደቀመዝሙር በሚለው ቃል ላይ አንድ ምሳሌ ላሳይ፦ ጶሊቃርጶስ በ70ዓ.ም ተወልዶ በ155 ዓ.ም ወይም በ160 ዓ.ም የሞተ የሐዋሪያው ዮሐንስ ደቀመዝሙር(ማቴቴስ/μαθητής) እንደነበር የቤተክርስቲያን የታሪክ መጻሕፍት ያወሱናል። በተጨማሪ ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአቴንስ ደግሞ ስሙም በሐዋ17:34 ላይ የተጠቀሰ ሲሆን ይህ የቤተክርስቲያን አባት ደግሞ የሐዋርያው ጳውሎስ ደቀመዝሙር (ማቴቴስ/μαθητής) እንደነበር ይነገራል። ይህ ማለት ጶሊቃርጶስ የሐዋርያው ዩሐንስ ተከታይ ሲሆን፤ ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአቴንስ የቅዱስ ጳውሎስ  ደቀመዝሙር እንደሆነና የአስተማሪያቸው ማቴቴስ ተብለው መጠራታቸውም ከታሪክ ክታባት እንረዳለን። በአንዳንድ የሙስሊም ተሟጋቾች የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርት እንዲሆኑ እንጂ ክርስቲያን እንዲሆኑ ኢየሱስ ሐዋርያትን አላዘዘም ይላሉ። ነገር ግን የክርስቶስ ደቀመዝሙር ማለት እና ክርስቲያን ከሚለው ቃል ጋር ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ ደቀመዛሙርቴ ካለ( ዮሐ 15:8፣ 13:35፣ ማር 14:14፣ ሉቃ 22:11፣ ማቴ 26:18…) የእርሱ ተከታይ(ክርስቲያን) መሆናቸውን ምንም ሳናቅማማ እንቀበላለን ማለት ነው። ስለ ክርስትና እና ደቀመዝሙር ይህን ያህል ካየን ነብያቱ ክርስቲያን ነበሩ ወይ? ክርስቲያን ከነበሩስ ምንድነው ማስረጃቹ? የሚለውን በመመለስ እንዝለቅ። የክርስቶስ ምስክርነት በማቴዎስ ወንጌል 5፡3-13 ላይ በተለምዶ ይህ ክፍል የተራራው ስብከት በመባል የሚታወቅ ሲሆን ሙሉ ዐውደ ምልከታ እያነበባቹ ስትወርዱ ቁጥር 11-12 ላይ አንድ አስደናቂ ንግግር እንመለከታለን እንዲህ ይላል፦ “ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ።”  ማቴዎስ 5፥11 እዚህ ክፍል ላይ ኢየሱስ እርሱን በመከተላቸው ስለሚደርስባቸው ነቀፌታ፣ ስደትና ችግር ሁሉ መፍራት እንደሌለባቸው፤ ጨምሮም ብፁዓን እንደሆኑ ይነግራቸዋል። ስደቱም በክርስቶስ ያለ መሆኑን በቁጥር 11 ላይ በእኔ ምክንያት የሚል ንግግር ያስቀምጣል። በዚህም አላበቃም ይቀጥልና በቁጥር 12 ላይ እንዲህ ይለናል፦ “ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና።”  ማቴዎስ 5፥12 ክርስቶስን የሚከተሉ ሰዎች ዋጋቸው ታላቅ እንደሆነ! እርሱንም መከተል የዚህ ስደት እና እንግልት ከንቱ እንዳልሆነ፤ ይልቁንም “ከእናተ በፊት የነበሩትን ነብያቶች እንዲሁ አሳድዷቸዋልና በማለት በረከቱን ይነግራቸዋል። ምክንያቱም በክፍሉ ዐውድ ሲብራራ እነርሱ ተነቅፈዋል፣ ያላቸው ነገር አጥተዋል፣ ስለ እርሱ ሲሉ መረባቸውን ጥለው ተከትለውታል መሠደዱ እና ማጣቱ “በእኔ ምክንያት ነው ይላቸዋል” ነገር ግን እኔን መከተላችሁ ከንቱ አይደለም፤ ብሎ ይቀጥልና፦ ከእናተ በፊት የነበሩትን ነብያት እንዲሁ አሳድዷቸዋልና በማለት ከቀድሞ ነብያት ጋር አገናኝቶት የቀድሞዎቹም መሠደዳቸው በእርሱ መሆኑን ይነግራቸዋል። በተጨማሪም በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 23፥34-37 ላይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የኦሪት ህግ መምህራንን እና ፈሪሳውያንን ሲነቅፍ እንዲህ ብሎ ሲናገር እንመለከታለን፦ ማቴዎስ 23 ³⁴ ስለዚህ፥ እነሆ፥ ነቢያትንና ጥበበኞችን ጻፎችንም ወደ እናንተ እልካለሁ፤ ከእነርሱም ትገድላላችሁ ትሰቅሉማላችሁ፥ ከእነርሱም በምኵራባችሁ ትገርፋላችሁ ከከተማም ወደ ከተማ ታሳድዳላችሁ፤³⁵ ከጻድቁ ከአቤል ደም ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከ ገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ።³⁶ እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ በዚህ ትውልድ ላይ ይደርሳል።³⁷ ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም። ትኩረት ሰጥታቹ ተመልከቱ፤ ቅዱሱም ማቴዎስ የክርስቶስን ንግግር አጽንዖት ሰጥቶ ነው እየጻፈልን ያለው። የጌታችን የኢየሱስ ንግግርም ዝም ብሎ ሀይለ ቃል አይደለም ይልቁን የርዕሳችን ዋና ማገር እንጂ። እንዲህ ነው ነገሩ፦ ጌታችን እሱን ባለመቀበላቸው የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች በራሳቸው ላይ ሊደርስባቸው ያለውን መከራ ተናግሯል ነገር ግን ከዛ መከራ ያርፉ ዘንድ ዶሮ በክንፎቿ ስር እንደ ምትሰበስብ ሲጠራቸው እንመለከታለን። በዛው ክፍል ላይ፦ “እኔ ወደ እናንተ ነቢያትን እልካለሁ” ስለዚህ ያለ ጥርጥር እዚህ ነብያትንን፣ ሐዋርያትን እና ሌሎች የእሱን ተከታዮች መሆኑን እየገለፀ ነው። ይህ ማለት ምን ማለት ነው? በድጋሚ ወደ ማቴዎስ ተመልሳቹ ጌታችን የተናገረውን እና ያለውን አስተውሉ፦ “ከአቤል…እስከ ዘካሪያስ” ስለ አቤል ሞት ተጽፎ የሚገኘው በዘፍ 4፥8 ላይ ሲሆን፣ ስለ ዮዳሄ ልጅ ስለ ዘካሪያስ ሞት ደግሞ በ2ዜና 24፥20-22 ተጽፏል። ጌታችን ኢየሱስ በዚህ ላይ ምን እያለ ነው ከተባለ በአይሁድ የቅዱሳት መጻሕፍት ቅደም ተከተል መሠረት፣ መጽሐፈ ዜና መዋዕል የብሉይ የመጨረሻ መጽሐፍ ነው። “ከአቤል እስከ ዘካሪያስ” የሚለው አባባል እኛ “ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ” ከምንለው ጋር ተመሳሳይ ነው። ታዲያ ጌታችን ይህን ሀይለ ቃል መጠቀሙ የብሉይ አጠቃላይ ሰማዕታን የሆኑ መልዕክተኞች እርሱ እንደላካቸው ማስገንዘቡን እንመለከታለን። አስተውሉ እኔ ልኬ ነበር ገደላችሁ እያላቸው ነው። የትኛው ነብይ እንዲህ ሊናገር ይችላል? ለዚህም ነው ከጌታችን ንግግር ተነስተን ኢየሱስ ያህዌ ነው፣ የቀድሞም ነብያት እርሱን ሲከተሉ ነበር የምንለው። የእነዚህ ክፍል ማብራሪያ ከሌሎች ቅዱሳት መጽሐፍት ጋር በማመሳከር ከእነርሱ(ከሐዋርያቶቹ) በፊት የነበሩት ነቢያትና የእምነት አባቶች ጨምሮ ክርስቶስን እንደተከተሉ ስለ እርሱም ሲሉ መከራን እንደተቀበሉ እናም እንደተነቀፉ ከዚህ በመቀጠል በቅድመ ተከተል እንመለከታለን። የሌሎች ሰዎች ምስክርነት ቅዱሳት መጻሕፍት ከዚህ ርዕስ አንፃር ምን ያስተምራሉ? የሚለውን ለመመለስ በዕብራውያን መልዕክት ምዕራፍ 11:1-40 ያለውን መመልከት ለዚህ ጥያቄ ጥሩ ምላሽ የምናገኝ ይሆናል። በዚህ የታሪክ ምዕራፍ ስለ እምነት አባቶች ከሚያወሳ ክፍል ከሆነው ዕብራውያን ምዕራፍ 11:25-26 የሙሴ ያሳለፈው የህይወት ውጣውረድ እንዲህ እንዲህ በማለት ያስቀምጣል፦ “ከግብፅም ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቦአልና ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ፤ ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና።”  — ዕብራውያን 11፥25-26 በደንብ አስተውሉ የዚህን ክፍል ጥቅስ ከማቴዎስ ወንጌል 5:11-12 ጋር ስናነፃፅረው ጥልቅ መልዕክት ይነግረናል። ከላይ በተራራው ስብከት ላይ እርሱን በመከተል ስለሚደርስ መከራ ከነገራቸው በኋላ በዚህም ሳያበቃ እነርሱ ብቻ ሳይሆኑ በእርሱ ምክንያት መከራው የበዛባቸው የቀድሞም ነቢያቶችም ጭምር በመከራ ውስጥ ማለፋቸውንና የቀኝ እጃቸውን አሻራ አሳርፈው እንዳለፉ ይነግረናል። ታዲያ ከቀድሞ ነብያት ውስጥ ታላቁ ነቢይ የነበረው ሙሴ <<ከግብፅ ጮማ እና ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መከራን መቀበል>> እንደመረጠ የዕብራውያን መጽሐፍ ይነግረናል። ስለዚህ ክርስቲያን በሚለው የቃሉ ትርጓሜ መሠረት በመነሳት ከቀድሞ ነብያት ውስጥ ሙሴ ክርስቲያን ማለትም የክርስቶስ ደቀመዝሙር (μαθητής/ማቴቴስ) እንደነበረ እንመለከታለን ማለት ነው። ታዲያ ታላቁ የብሉይ ኪዳን ነቢይ ሙሴ እንዴት ሆኖ ነው ክርስቶስን ተከትሎ ሙስሊም የሚሆነው? ሙስሊም ማለትስ ክርስቶስን መከተል ነውን? መልሱን ለአንባቢ ልተወው። የዕብራውያን መልዕክት ጸሐፊ በዚህ አላበቃም ተጨማሪ ጥልቅ ጠቢብ ሚስጥር እንዲህ በማለት ለተደራሲያኑ ይገልፅላቸዋል፦ “እነዚህም ሁሉ በእምነታቸው ተመስክሮላቸው ሳሉ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አላገኙም፥ ያለ እኛ ፍጹማን እንዳይሆኑ እግዚአብሔር ስለ እኛ አንዳች የሚበልጥ ነገርን አስቀድሞ አይቶ ነበርና።”  ዕብራውያን 11፥39-40 እነዚህ ሁሉ የተባሉት በቁጥር 38 ላይ በጠቅላላ ለመተረክ ጊዜ ያጥረኛል ያላቸውን መሆኑን በክፍሉ ዐውደ ምንባቤ ላይ መረዳት ይቻላል። ከላይ ባለው ጥቅስ በመጨረሻ ቁጥር ስር

የቀድሞ ነብያት ክርስቲያን አልነበሩምን? Read More »

የዮሐንስ ወንጌል አጭር ሐተታ

መግቢያ ➥የዮሐንስ ወንጌል በዘመናት መሐል በቤተክርስቲያን ተወዳጅነቱን ጠብቆ የቆየ መጽሃፍ ሲሆን በሌሎች ለዘብተኛ ምሁራን ደግሞ “አራተኛው ወንጌል” በመባል ይጠራል። ከጥንታዊት ቤተክርስቲያን አባቶች መካከል አንዱ የሆነው ቀለሜንጦስ ዘእስክንድሪያ ደግሞ መንፈሳዊ ወንጌል በማለት አቆላምጦታል [1]፤ ይህንን ያለበትም ምክኒያት ዮሃንስ ወንጌሉን የጻፈው በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነት ነው ብሎ ስላመነ እንደነበር የአውሳብዮስ ዘቂሳርያ ዘገባ ያሳያል። ወንጌሉ ምንም ያህል አከራካሪ ጉዳዮች ቢኖሩበት፤ ከዘመናውያኑ ሥነ መለኮት ምሁራን አንዱ የሆነው ኮሊን ክሩዝ ደግሞ “ኁልቆ መሳፍርት ለሌላቸው የክርስትና ትውልዶች መነሳሳት የፈጠረና በስርዓት ላጠኑት ሁሉ ታላላቅ ሽልማቶችን ያስታቀፈ” [2] በማለት መስክሮለታል። የጸሃፊው ማንነት ➥የወንጌሉን ትክክለኛ ጸሃፊ በተመለከተ የተለያዩ አመለካከቶች ቢኖሩም በሐዋርያው ዮሃንስ ስለመጻፉ የሚቀርቡ ሃሳቦች ከሌሎች ይልቅ ተጨባጭነት አላቸው። በቅድሚያ የመጽሃፉን ውስጣዊ ማስረጃዎች (internal evidences) እንመልከት። ጸሃፊው የአረማይክ ቋንቋ ችሎታ ያለው አይሁዳዊ ስለመሆኑ ለሚጠቅሳቸው አንዳንድ የእብራይስጥና አራማይክ ቃላት ትርጉም ማስቀመጡ ምስክር ነው፤ የአይሁድን ወግና ስርአት ጠንቅቆ የሚያውቅ ሰው መሆኑን የገዛ ጽሁፉ ያሳያል (ዮሃ 4፡ 9፣ 20)፤ ስለ መጀመሪያው ክፍለ ዘመን የእስራኤል መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ በትክክል እንደሚያውቅም ከወንጌሉ ላይ መረዳት ይቻላል (ዮሃ 1፡44፣ 2፡1፣ 4፡5፣ 4፡21፣ 9፡7፣ 11፡18፣ 18፡1)፤ እንደዚሁም የአይን ምስክርና የኢየሱስ የቅርብና ተወዳጅ ሰው እንደነበርም ይናገራል (ዮሃ 1፡14፣ 19፡35) [3]።ከኢየሱስ የቅርብ ደቀ መዛሙርት መሃል ያዕቆብ ብዙም ሳይቆይ ስለሞተ፤ እንዲሁም ጴጥሮስ ቶማስና ፊሊጶስ በሶስተኛ መደብ እየተጠሩ ስለተዘገቡ የጸሃፊው ማንነት ዮሃንስ የመሆኑ እውነታ የበለጠ ተአማኒነት አግኝቶአል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪ ያሉ ማስረጃዎችን (External Evidences) በአጭሩ ስንዳስስ ደግሞ የጥንት የቤተክርስቲያን አባቶችን ምስክርነት እናገኛለን።ከላይ እንደተመለከትነው አውሳብዮስ ዘቂሳርያ በዘገበው መሠረት የእስክንድርያው ቀለሜንጦስ ይህንን ወንጌል መንፈሳዊ ወንጌል ብሎ ጠርቶታል። ቀለሜንጦስ ወንጌሉን በዚህ ስም የጠራውም ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈው በደቀ መዛሙርት ተገፋፍቶና በመንፈስ ቅዱስ ተነሳስቶ እንደሆነ በማመኑ እንደነበረ አውሳብዮስ ጨምሮ ዘግቧል [4]። በመሆኑም ቀለሜንጦስ አራተኛው ወንጌል የተጻፈው በሐዋርያው ዮሐንስ እንደሆነ ያምን ነበር። 200 ዓ.ም አካባቢ እንደጻፈ የሚገመተው ኢራኒየስ ወንጌሉን የጻፈው የተወደደው ደቀ መዝሙር ዮሐንስ መሆኑንና የጻፈውም በኤፌሶን ሳለ እንደነበረ ተናግሯል [5]። በተጨማሪም የተወሰኑትን የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ዝርዝር ይዞ የተገኘውና ከ 180-200 ዓ.ም ድረስ እንደተጻፈ የሚገመተው የሙራቶሪያን ጽሁፍ አራተኛውን ወንጌል በዮሐንስ እንደተጻፈ ይመሰክራል። ዮሐንስ ወንጌሉን እንዴት ጻፈው? ለሚለው ጥያቄ ይህ ጽሁፍ ተአማኒ ዝርዝር ባይኖረውም ወንጌሉ በተጻፈባቸው አመታት ውስጥ ጸሃፊው ዮሐንስ መሆኑ ይታመንበት እንደነበር ያሳያል [6]። በመሆኑም ከውስጣዊ ማስረጃዎች ጸሃፊው ፍልስጤም ምድር ውስጥ የሚኖር አይሁዳዊ መሆኑን፣ የኢየሱስ የአይን ምስክር መሆኑን፣ከአስራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ መሆኑንና ከጽሁፉ ዝርዝሮች በመነሳት ጸሃፊው ዮሐንስ እንደሆነ መገመት እንደሚቻል ስንረዳ ከውጫዊ ማስረጃዎች ደግሞ ወንጌሉ ለተጻፈበት ዘመን የሚቀርቡ አባቶችና ተጨማሪ ጽሁፎች የዮሐንስን ጸሐፊነት እንደሚደግፉ መገንዘብ ይቻላል። የዮሐንስ ወንጌል በራሱ በዮሐንስ መጻፉን የሚጠራጠሩ ምሁራን ቢኖሩም ከላይ ባነሳናቸው ማስረጃዎች መሠረት ጸሃፊው ሐዋርያው ዮሐንስ መሆኑን ተቃውሞ በብቃት የሚቆምና ተለዋጭ ጸሃፊ በርግጠኝነት የሚያቀርብ መከራከሪያ ግን ሊገኝ አልቻለም። የተጻፈበት ዘመንና ስፍራ ➥ልክ እንደ ጸሃፊው ማንነት ሁሉ በዘመናችን ምሁራን ዘንድ ወንጌሉ መቼ እንደተጻፈ የማያባራ ክርክር ይደረጋል። አንዳንዶች የተጻፈው በ2ኛው ክፍለ ዘመን መካከለኛ አመታት፤ ማለትም 150 ዓ.ም አካባቢ እንደሆነ በማንሳት ይከራከራሉ። ይሁን እንጂ የሥነ ቁፋሮ (Archaeology) ጥናቶች የሚያሳዩት የዮሐንስ ወንጌል የተጻፈው በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ መሆኑን ነው። የዮሐንስ ወንጌል የመጀመሪያው እደ-ክታብ Papyrus 52 የሚባል ሲሆን የምዕራፍ 18ን የተወሰኑ ክፍሎች የያዘና በ130 ዓ.ም አካባቢ እንደተጻፈ የሚገመት ቁራጭ ብራና ነው። ቀጥሎም ከምዕራፍ 1-14 ድረስ ያለውን አብዛኛውን ክፍልና የቀሩትን ምዕራፎች በከፊል የያዘው Papyrus 66፤ እንዲሁም ከምእራፍ 1-11 እና ከ12-15 ድረስ የያዘው Papyrus 75 ከጥንታዊ እደ ክታባት ይመደባሉ። እነዚህ እደ ክታባት ከሁለተኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ይመዘዛሉ [7]። እንግዲህ እስካሁን የሚታወቀው የመጀመሪያው የወንጌሉ ቅጂ (P 52) የተጻፈው እንደተገመተው በ 130 አካባቢ ከነበረ የመጀመሪያው ጽሁፍ የተጻፈው በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን መሆኑ ግድ ነው። ወንጌሉ የት ተጻፈ? ለሚለው ጥያቄ ደግሞ በቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያንና በኢራንየስ ትውፊቶች ላይ መደገፍ ግድ ይለናል። ቀለሜንጦስ እንደጻፈው ዮሐንስ ከፍጥሞ ደሴቱ ስደት ወደ ኤፌሶን የተመለሰው ንጉሡ ዶሚሽያን ከሞተ በኋላ (ከ 81-96) ሲሆን ኢራኒየስ ደግሞ ሐዋርያው እስከ ትራጃን ንግስና ዘመን ድረስ (ከ98-117) እዚያው ኤፌሶን እንደነበረ ይናገራል [8]። ይህም ወንጌሉን በዚያ ጊዜ (በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን መጨረሻ) በኤፌሶን ሳለ ጽፎታል የሚል ግምትን አሳድሯል። ስለዚህም የዮሐንስ ወንጌል ከ80-90 ዓ.ም ሐዋርያው ዮሐንስ በኤፌሶን ሳለ የጻፈው ወንጌል መሆኑ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት አለው። የዮሐንስ ወንጌል ዋና ዋና ይዘቶች ➥በመጀመሪያው ምእራፉ ስለዋና ገጸ ባህርዩ ማንነት በዝርዝር ይናገራል። ይህም ገጸ ባህርይ በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር ጋርየነበረው በፍጥረት ስራ ላይ ተሳታፊ የነበረውና በኋላም ሰው ሆኖ የመጣው ኢየሱስ መሆኑን ይናገራል። ➥እስከ ምእራፍ 12 ድረስ ሰፋ ባሉ ንግግሮችና በተአምራት የተገለጠውንና በልጁ ለሚያምኑ ሁሉ የዘለአለም ህይወት የሚሰጥአባቱን የተረከውን ኢየሱስን በተዋበ የመክፈቻ ንግግር መልክ እናገኛለን። ➥ከምእራፍ 13 – 20 ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለቀጣይ ዘመናት ሲያዘጋጅ፣ ሲመክራቸውና ሲጸልይላቸው፣ እንዲሁም ስቃዩን፣ ስቅለቱንና ሞቱን እንዲሁም ትንሳኤውን ያስቃኘናል። ➥ምእራፍ 21 ተጨማሪ የትንሳኤውን ምስክርነቶች፣ ለጴጥሮስ የተሰጠውን ተልአኮ ከሞቱ ትንበያ ጋር፣ እንዲሁም የተወደደውን ደቀ መዝሙር ምስክርነት ያስቃኘናል [9]። የዮሃንስ ወንጌል ልዩ ባህርያት ➥በሶስቱ ተመሳሳይ ወንጌላት ዘገባ የኢየሱስ አገልግሎት ትኩረት ያደረገው በገሊላ ሲሆን የዮሃንስ ወንጌል ግን በብዛት የኢየሱስን የይሁዳና የኢየሩሳሌም አገልግሎት ያስቃኘናል። ተመሳሳዮቹ ወንጌላት የኢየሱስን ምሳሌያዊ ንግግሮች፣ የእግዚአብሔርን መንግስት የተመለከቱ ስብከቶቹን፣ እንዲሁም በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ያደረጋቸውን ንግግሮች (ለምሳሌ ስለ ምጽዋት፣ ስለጋብቻና ፍቺ፣ ስለግብር ስለጭንቀት፣ ስለሃብት፣ ወዘተ…) ሲያስነብቡን የዮሃንስ ወንጌል ግን “እኔ… ነኝ” በሚሉ ሃረጋት በሚጀምሩ ኢየሱስ ስለራሱ በተናገራቸው ንግግሮች ይታወቃል። የዮሃንስ ወንጌሉ የኢየሱስ ንግግር ከሶስቱ ተመሳሳይ ወንጌላት በተለየ ከላይና ከታች፣ ብርሃንና ጨለማ… ወዘተ በሚል ሁለት ነገሮችን በተነጻጻሪነት በሚመለከት አጻጻፉ ይታወቃል። በዮሃንስ ወንጌል በተዘገበው የኢየሱስ አገልግሎት የሚገኙት ክስተቶች በሌሎቹ ወንጌላት ውስጥ አይገኙም። ማለትም የወይኑ ተአምር (2: 1-11)፣ ከኒቆዲሞስ ጋር ያደረገው ጭውውት (3:1-13)፣ የሳምራዊቷ ሴት ታሪክ (4:1-42)፣ የቤተዛታው ኩሬ ፈውስ (5:1-18)፣ የሰሊሆም መጠመቂያው ፈውስ (ምእራፍ 9)፣ የአላዛር ከሞት መነሳት (ምእራፍ 11)፣ ኢየሱስ የደቀ መዛሙርቱን እግር ማጠቡ (13: 1-11)፣ እንዲሁም ኢየሱስና ጲላጦስ ያደረጉት ዘለግ ያለ ንግግር (18:28-19:22) የሚገኙት በዮሃንስ ወንጌል ብቻ ነው [10] የዮሐንስ ወንጌል ስነ መለኮት ➥የዮሐንስ ወንጌል በውስጡ ብርሃንና ጨለማ፣ ሞትና ህይወት የሚሉ ሐሳቦች በተነጻጻሪነት ተደጋግመው ተነስተዋል፤ ይህም የኖስቲክ እሳቤን የያዘ ወንጌል እንደሆነ እንዲታሰብ ምክንያት ሆኗል። ነገር ግን የኖስቲክ መምህራን ስጋን ሁሉ እንደ እርኩስ ነገር ስለሚቆጥሩ አምላክ በስጋ እንደመጣ የሚናገረው የዮሐንስ ወንጌል ከእነርሱ አስተምህሮ በተቃራኒ እንደሚቆም ለመረዳት አይከብድም[11]። ይህ ወንጌል ልዩ የሆነ ነገረ ክርስቶስን ይዟል፤ ይህንንም ኢየሱስ አባቱን ለመተረክ ከሰማይ የመጣ፤ ተግባሩንም ተወጥቶ ወደመጣበት የተመለሰ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በአግባቡ በማሳየት ገልጦታል። (ዮሐ 1:18፣ 3:13፣ 6፡33፣ 38)። በስጋ የተገለጠ አምላክ የሚልን ነገረ ክርስቶስ በዋናነት የምናገኘውም እዚሁ ወንጌል ውስጥ ነው። መንፈስ ቅዱስ በታሪካዊው ክርስቶስ (Historical Jesus) የተገለጠውን እውነት ወደ አማኞች በማምጣት ተግባሩ ተገልጧል። የዩሐንስ ወንጌል በቃልና በስራ ለእግዚአብሔር የመታዘዝን ስነ ምግባር በኢየሱስ በኩል ያስተምራል። ዋናውን የኢየሱስን ትእዛዝ ፍቅርንና ትህትናን በአማኞች መሃል ያስተዋውቃል (ዮሐ 13:14)። ይህንንም ኢየሱስ ራሱ በተግባር በማድረግ አስተምሯል (ዮሐ 15:12-14) [12] ወንጌሉ የተጻፈበት አላማ ➥ለዚህ ጥያቄ እንደ መልስ የሚቀርበው የመጀመሪያው መላ ምት ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈው ለሶስቱ ወንጌላት ተጨማሪ ድጋፍ ይሆን ዘንድ ነው ይላል። በዚህ መላ ምት መሠረት ሐዋርያው ከእርሱ በፊት የተጻፉትን ሶስቱን ወንጌላት በተመለከተ ጊዜ ይዘታቸው አላረካውም፤ ስለዚህም ወንጌሉን በዚህ መልኩ ጻፈው። ነገር ግን ወንጌሉ በሶስቱ ወንጌላት ላይ ጥገኝነት ባለማሳየቱ ይህ

የዮሐንስ ወንጌል አጭር ሐተታ Read More »

የጥንቱን ሃይማኖት!

የዚህን ታላቅ ፕሮቴስታንት ሐዳሲ ንግግር ያስተዋለ የትኛውም በፕሮቴስታንት ጥላ ውስጥ ያለ ሰው በቀጣይ ሚያስተውለው ወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት የገቡበትን ችግር ታሪካዊነቱ ቀርቶ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆነ የአምልኮ ስርአት ችግር ነው።[ይህ ችግር በተለያዩ ቦታዎች የሚደረጉ ቅጥ ያጣ ፈንጠዝያን ጨምሮ የሚያካትት ነው።] ይህን ችግር ግን በታሪካዊው ወይም በክላሲካል ፕሮቴስታንት መነጽር ስናየው የቀድሞው መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ባለው በቤተክርስቲያናዊ አስተምህሮ የበለጠገ አምልኮ እንዲሁም ለእነዚህ ቅጥ ላጡ አካላት እጅግ የታመነ የእምነት አቋም እንዳለው ቢታወቅም ልንክድ ማንችለው እውነት ግን ወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ውስጥ ሚታየው ስረአት አልባ የአምልኮ ስርአት አግባብ ያልሆነ ብቻ ሳይሆን እጅግ ስህተት የሆነ ልምምድ መሆኑን ነው።(መታረምና መታየት ያለበት መሆኑን ይህ ጽሑፍ አጥብቆ ይናገራል) እንዲያው የዚህን ጉዳይ ጉድለት ትኩረት ሰጥተን ብንመለከተው ችግር ሆኖ ምናገኘው የእውነት ጉድለት ሳይሆን፥ ለድህረ ዘመናዊነት እጅግ የተጋለጥን መሆናችን፣ ቃሉን ሳይረዱት “ሃይማኖት አያድንም” የሚሉና የአስተምህሮን አስፈላጊነት የጣሉ ሰባኪያንና መምህራንን በተሃድሶው ክርስቲያን ማህበረሰብ ዘንድ ምስባክ ላይ ማቅረባችን፤ ይህንንም ተከትሎ አጥንትን ከመጋጥ ይልቅ ወተት መጋትን የሚወድ፣ በእምነቱ በቆየበት ልክ እውቀትንና ብስለትን ያጣ ምእመን ማፍራታችን ለዚህም የልጆች ፈንጠዝያ ሥርአተ አምልኮ መፍያና ማሟያ እንዲሆኑ ጆሮአችንን ለማከክ የፈቀዱን ሰዎች መሪዎችና እረኞች እንዲሁም መጋቢያን ዝም ማለታቸው ነው።(አጥብቀው የሚቃወሙና አጥብቀው የሚገስጹ እንዳሉ መዘንጋት የለብንም) መፍትሔ፦ መፍትሔው ሐዳሲያኑ የቆሙበትንና እኛም የተነሳንበትን እውነት አለመጣል ነው። ምክንያቱም ጌታን ለምን እንደተከተልነው እናውቅ ዘንድ ይገባናልና። ስለዚህ እውነትን በሙላት ልንካፈል እንጂ እምነትን አስታከን ለወደቀው አዳማዊ ማንነታችን ነፃነትን በመስጠት አለማዊነትን ልንለማመድ አይደለም። መሰረታችና አስተምህሮአችን የሆነው“የእግዚአብሔር ቃል ብቻ” “የእምነት መግለጫችንም” ብቻ ሳይሆኑ ምስባኮቻችንን፣ ልምምዶቻችንንና አምልኮአችንን የቆምንበት እውነት ሊገልጹ ይገባል። የዚህ ችግር ጉዳት “ውሃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው” እንዲሉ አበው እንደ ምእራባዊያን ሳይታወቀን ቀስ እያልን ለዘብተኞች እንዳንሆን። ወንድምና እህት ክርስቲያኖች ሁላችን ለምን እንደተጠራን ካወቅን እንግዲህ እንንቃ። ከራሳችን፣ ከቤተክርስቲያን ጣዕመ ዜማ ካለው አምልኮ፣ ከቅዱሳን ስብስብ(ማህበር) አስበልጠን የተሸከምነውን አለማዊነትንና ለአለማዊነት ያዘመመን ለዘብተኛ ክርስትናን ፈፅመን እናስወግድ፥ ማን እንደሆንን እናውቃለንና። ➠ የተሐድሶአችን ጥሪ ወደቀደመው እምነት እንመለስ እንደሆነ ሁሉ፥[2] ➠ እንደ ቀድሞው የአምልኮአችንን ማእከል፥ ቅዱሳት ምስጢራትንና የእግዚአብሔርን ቃል መሠረታችን እናድርግ። ➠ ሥላሴያዊ የሆኑ መዝሙሮችና ስብከቶች ስርአትና ልምምድ ይሁኑልን፥ ➠ እንደ እምነታችን እንዘምር፣ እንስበክ፣ እናስተምር። ይህ ሁሉ ሲሆን በመንፈስ ቅዱስ ሃይል፥ በልጁም በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል ለእግዚአብሔር አብ ክብር ይሆን ዘንድ። ቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሳርያ በእንተ መንፈስ ቅዱስ መጽሐፉ ላይ፦ “…ቤተ ክርስቲያን የጠበቀችው ሐይማኖት በሐዋርያት የተላለፈውን ነው፣ የተቀበልነው እንዳናጠፋ ከአባቶች እምነት ጋር ጸንተን እንኑር !..” በማለት የተሐድሶ አበው እንዳስቀመጡት ባስልዮስ ያስቅምጠዋል። ታዲያ ቤተክርስቲያን ከዚህች ወጥመድ ታመልጥ ዘንድ የተሐድሶውን ወቅት በማየት መነጽራችንን ወደ ቀደመው አምልኮዎቻን እንመለስ ስንል ይህን ጽሑፍ እንቋጫለን። በአሚነ ሥላሴ ያጽናን። አሜን! ማጣቀሻ [1] The first book of discipline, Volume 3 page 34 [2] ተሐድሶ ማለት አዲስ ክርስትና መመሥረትና መቀጠል አይደለም። ይልቅ ወደ ቀደመው ውብ ክርስትና ቃሉ ብቻ የበላይ ወደ ሆነባት ክርስትና እንመለስ እንጂ።

የጥንቱን ሃይማኖት! Read More »

መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን እንጠያየቅ – ክፍል 2

ጥያቄ፦ እሺ ይሄን ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ያልከውን እንደ ሙግትህ ልቀበልህና መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ እየተባለ የተለያየ ሥነ-አፈታት ላይ የተለያየ ምልከታ ትደርሳላችሁ? ለዚህ ስነ አፈታት ዳኛችሁ ማነው? መልስ፦ በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው። ይሄ እኮ ጥያቄ ቢነሳ በእናተም ዘንድ ያለ ነው።(ትውፊት ያላችሁ እናተም ይሄንን ተመሳሳይ ክሌም ማንሳት እንችላለን።) እኛ ነገሩን ሥነ መለኮታዊ ክፍፍሎሽ(Theological Triage) ብንሰራለት እንኳን። ወደፊት የማስረዳህ ይሆናል። አሁን ግን ወደ ጥያቄህ መልስ ልለፍልህ። ጥያቄ፦ እሺ መልስ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ እያላችሁ ሥነ አፈታት ላይ ብዙ ትለያያላችሁ። የሚል ጥያቄ ነው የተነሳው። ያው የሥነ-አፈታት መርሖ በመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ መነጸር ሲታይ የራሱ የሆነ መንገድን አለው። ለሶላ ስክሪፕቹራ አማኝ መጠየቅ የሌለብህና ማሶገድ ያለብህ ጥያቄ፦ ስህተት1፦ እንደው ሰው እንደፈለገ እየፈታ እየተረጎመ መጠቀም አለበት የሚል እሳቤ አለው። ስህተት2፦ የመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ችግር ይሄን ያስከትላል። ስህተት1 እና ስህተት2፦ የሁለታችሁ ዳኛችሁ ማነው ታዲያ? ለስህተት1 እና ለስህተት2 ድምዳሜህ ምላሻችን፦ መልስ፦ እነዚህ ነገሮች ለመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ አማኝ ለሆነ ሰው የሚቀርብ ጥያቄ ነው ብዬ አላምንም።[እንዴት የሚለውን ወደ በኋላ እናየዋለን] ታዲያ ለዚህ መነሾ የመጀመሪያው መፍትሄ መርሕ የምንለው የሥነ አፈታት መርሖ በመባል ይታወቃል። ይህ ደግሞ አንደኛው መንገድ ነው(አውዳዊ ንባብ ንፅፅራዊ ምልከታ ነው።) ጥያቄ፦ ቆይ ቆይ ይህንን ታዲያ ሌላኛው ጎራም እነሱም ክሌም ያደርጉታል ግላዊነት አይደለም ወይ? መልስ1፦ ጥሩ ጥያቄ ነው። ግን የተሳሳትከው ነገር በተለይ በተለይ HGL(ጽሑፋዊ፣ ሰዋሰዋዊ እና ታሪካዊ ዳሰሳ) እንደነ ዲኤ ካርሰን የመሳሰሉ ምሑራን ይህ አይነቱ ትርጓሜ መጠቀም ይበልጥ ከግላዊነት ይልቅ ወደ ጽኑ ትርጓሜ እንደሚያመጣ ያስረዳሉ። ምክንያቱም ይሄ አይነቱ መንገድ ሥነ አፈታቱ በአውዱ ሲታይ፦ ➙ አውዳዊ ያልሆነው ተሟጋችህ ይወድቃል ➙ ከዛም ሻገር ስትል ሰዋሰዋዊ መንገድ በመጠቀም ታርመዋለህ፣ ➙ታሪካዊ መንገድን ትጠቀማለህ። ይሄ አይነቱ ሥነ አፈታት ለግላዊነት ወጥመድ ነው ማለት የማይቻልበትን መንገድ ቀጣይ ከማነሳቸው ካልኩህ ጋር አያይዤ አቀርባቸዋለሁ። መልስ 2፦ ሌላው በእነ R.C Sproul እና John Piper ተቀባይነት ያለው ሲሆን ይህህም መንፈሳዊውን ትርጓሜ ነው። ይሄ የሚወሰደው በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ነው። እንደ R.C Sproul እና John Piper አይነቱ የሚሉት መንፈስ ቅዱስ ለመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ እንዳንስት ትልቁን ሚና በአማኞች ዘንድ ከጥናት አንጻር እንደሚሰራ ይናገራሉ። ➙ ታሪካዊ የጉባኤዎች ውሳኔ እና መግለጫዎች ለሥነ አፈታት ቀጥተኛ ተዛምዶ ባይኖራቸውም(ማለትም በእነርሱ ተጠቅሞ በቀጥታ መተርጎምን ማድረግ ባይችሉም) በሉተራኑ ሥነመለኮቱ ላይ ባሉ እንደነ Robert Kolb እንደሚሉት ክሪዶች እና ኮንፌሽኖች ለመጽሐፍ ቅዱስ ስነ አፈታት አቅጣጫ ጠቋሚዎች ናቸው ይላሉ። ይህም ለቅዱሳት መጻሕፍት የበላይ ባለሥልጣንነት እንዲሁም በቂ እንደ መረታዊ አስተምህሮ ማለታችንም ነው። መልስ 3፦ በሥነ አፈታት ላይ ጥያቄህን በመራሕያነ ተሐድሶዎች በኩል ዘንድ የሚነሱ ሙግቶች ቢሆኑ ለምሳሌ፦ ካልቪኒዝም እና አርሜኒያን የሚል ቢሆን በቀላሉ ከትውፊት ጋር ካልሆነ የምትሉም ራሳችሁ ተከፋፍላችሁ ሳለና ወደ አበው ጎራ መካከል ጠጋ ስንል ራሱ ከሥነ አፈታት ጀምሮ ሁለት አይነት ቤተ እውቀቶች አሉ ብሎ ሀሳብህን መሞገት ይችላል። ምክንያቱም በእስክንድርያ ያለው ቤተ እውቀት እና አንጾኪያ ያለው ቤተ እውቀት መካከል የሥነ አፈታት ልዩነቶች ይስተውላሉ። የእስክንድርያው አመስጥሮታዊ ፍቺ(allegorical interpretation) ሲጠቀም የአንጾኪያው ደግሞ ቁማዊ(literal) ይጠቀማል። በተለይ በነገረ ክርስቶስ ዶክትሪን አንጻር ከተመለከትነው ጎራ መደብ ልዩነቶች ይስተዋላሉ(Hypostatic Union & two nature of Christ)። የእኛ ጥያቄ የሚሆነው ስለዚህ የትኛው የትምህርት ቤተ እውቀት መጽሐፍ ቅዱሳዊውን ስነ አፈታት ተጠቅሟል? የሚባል ጥያቄ ቢነሳ በቀላሉ የሚታለፍ አይደለም።[ማንሳትም እንችላለን ለማለት ነው] ስለዚህ መልስ1፣ መልስ2 እና መልስ3 ሲቀመጡ፦ ድምዳሜ 1፦ ከላይ እንዳልነው በእኛ ምሑራን ዘንድ የሚባለው የቅዱሳት መጽሐፍ ትርጓሜ ከማንኛውም ግላዊነት የጸዳ መሆን ይኖርበታል። ነገር ግን በቤተክርስቲያን ታሪክ ስንመለከተው ሁለቱ ቤተ እውቀቶች ተጽዕኖ ያሳደረባቸው የየራሳቸው ነገሮች አላቸው። የእስክንድርያው ቤተ እውቀት(Alexandria school) ለምሳሌ በፕላቶኒዝም በሃይል የተጠቃ ሆኖ እናየዋለን። ለዚህም የእስክንድርያው አርጌንስ ስለ ነብስ የሚያብራራው ከባሲል ቄሳርያው ሊለይ ይችላል(የተለየም ነው) አርጌንስ ስለ ነብስ ያለውን ቴዎሪ ለጥጦ ፕላቶኒክ በሆነ መልኩ መጽሐፍ ቅዱስን መፍታትን ሊያደርግ ይችላል። ይሄም ደሞ ምናልባት ወደ ስህተት ሊያመጣውም ይችላል(ስለ soul የሰጠውን ኮንሰፕሽን ስለምናውቀው) ስለዚህ ነው ያለንበት አካባቢ ያስተማሩን ሰዎች ወይም የግል ምልከታ በራሱ ለመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ አፈታት መርህ ሆነው ይመጣሉ።[እንደውም የአበውን ሥልጣን ከመጽሐፍ ቅዱስ እኩል ካደረግነው ግላዊ ሥነ-አፈታት ሚነግስ አይደመስልህም?] ስለዚህ አንድ ትክክለኛ የሆነ የሥነ አፈታት መርሖ ያስፈልገናል። ይህም ሁሉም የሚዳኝበት HGL የምንለው መርህ ላይ አይመስልህም? ያው እንደ ጥያቄ ከተነሻ መወያየት እንችላለን ለማለት ነው። ድምዳሜ 2፦ ስለዚህ በሥርአት ከተጠናና ቋንቋውን እና ታሪካዊ አውዱ ከታየ ወደ ትክክለተኛው ሥነ አፈታት ይመራናል። መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ምንም እንኳን ግላዊን ትውውቅ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ያለንን ሕብረት ቢያበረታታም ከትርጓሜው እጅጉን ያርቀናል ማለት አይደለም። ስለዚህ በዶክትሪናል ነገሮች ሆኑ በአንዳንድ ውይይቶች ቤተክርስቲያን ውስጥ መታቀፍና ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመተርጎም አማኞች ተጠያቂ ቢሆኑ የሚልን ነገርን መርሳት የለብንም። ይሄም ደሞ ግላዊነትን ይቀንሳል። በተለይ እንደ አማኝ አጥብቀን መያዝ ያለብን መንፈሳዊው ላይ ነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለአማኞች የተላከው ለማስተማር ለማቅናት እና አቅጣጫን ለመስጠት እንደሆነ ሁሉ በጸሎት እና በትጋት በህብረትም ሆነ በግል በቤተ ክርስቲያን ጥላ ውስጥ የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ ጠቃሚ ነው እንላለን። ይህም የመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ አስተምህሮን አይቃረንም።

መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን እንጠያየቅ – ክፍል 2 Read More »

መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን እንጠያየቅ – ክፍል 1

ጥያቄ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን(Sola Scriptura) ተቀብሎ መቀጠል የቤተክርስቲያን ሥልጣናዊነትን እና የአበውን ጽሑፍ ባለስልጣንነትን እንዳንቀበል ያደርጋል። አይደል? መልስ፦ ኧረ በፍፁም! ይህን እንድንል ትንሽ ክፍተት እንኳን አይሰጠንም። ምክንያቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ብቻና አይሳሳቴው ባለስልጣን ነው የሚለው አስተምህሮ እነዚህን ጨምሮም ነው፦ ➙ ቤተክርስቲያን ባለስልጣን ነች። ➙ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ስንልም የአበው ክታባት ባለስልጣን አድርገን ነው። ይህን ስንል ግን ሊሳሳት የማይችልና የሁሉ መመዘኛ ባለስልጣን የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ መሆኑን አምነን ነው። ለዚህም ነው አውግስጢኖስ እንዲህ በማለት የተናገረው፦ If you discover in my writing anything false or blameworthy, you may know that it is bedewed by a human cloud, and you may attribute that to me as truly my own.[1] ስለዚህ እነዚህ መጻሕፍት ማለትም የአበው ክታባት ሕጸጽ ከሌለባቸው (infallible & inerrant) ከሆኑ ከቅዱሳት መጻሕፍት ቀጥሎ ክብር የሚሰጣቸው መጽሐፍት ናቸው። ጥያቄ፦ ለዚህ ንግግርህ የአዲስ ኪዳን ድጋፋት አለህ? መልስ፦ አዎ። ጌታ ኢየሱስ ካደረገው እና ካስተማረው ማሳየትና መጥቀስ ችላለሁ። ለምሳሌ፦ ማቴዎስ 23¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¹ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብሎ ነገራቸው፦² ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል። ጌታችን በማቴዎስ 23:2-3 በሙሴ ወንበር ላይ ስላሉ ጻፎችና ፈሪሳውያን ለተናገሩት ቃል ለቃላቸው መታዘዝ እንደሚገባ ያስተምራል።(ይሄም ደሞ በዘመኑ ሥልጣናዊ መሆናቸውን ያሳያል። ለዛም ሥልጣን መታዘዝ እንዳለብን ይናገራል።) ይህን አይተን ረሱ ጌታችን በማቴዎስ ምዕራፍ 15፥1-39 ላይ ጻፎች እና ፈሪሳውያን የደነገጓቸውን መመሪያዎች ከዋናው ከመጽሀፍ ቅዱስ ማዕከላዊ ትምህርት ጋር ስለተቃረኑ ይቃወማቸዋል።(ይህ ደሞ በመጀመሪያው ክፍለ ዘመናት ከመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን በላይ የሆነ ግዛት እንዴሌለ ያሳየናል። መልሴን በአጭሩ ሳስቀምጠው፦ መነሻ1፦ ጻሕፍት እና ፈሪሳውያን ሥልጣናዊ ናቸው። መነሻ2፦ ይህ አንድ አካል ሥልጣን አለው ማለት ግን የግድ ሊሳሳት የማይችል ሥልጣን(ከመጽሐፍ ቅዱስ እኩል የሆነ) ነው ማለት ግን ፈጽሞ አይቻልም። ስለዚህ ድምዳሜ1፦ ስለዚህ ይህ ሥልጣናዊው አካል ራሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ይመዘናል። ልክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳደረገው። ድምዳሜ2፦ እነዚህ መዛኞቹ ጌታችንን ራሱ የጠየቁት እና የመዘኑት በመጽሐፍ ቅዱስ መሆኑ የሚያሳየው በዘመኑ በእነርሱ አስተሳሰብ መጽሐፍ ቅዱስ የበላይ ባለስልጣን መሆኑን ጥቂት የሚያሳይ ፍንጭ ነው። በዚህ ክፍል ግን ጌታችን የበላይ ባለስልጣን ያደረገው ራሱ በነብያቱ በኩል የተናገረውን የራሱን ቃል በሕዝቡ ዘንድ ነው። በመጨረሻም ድምዳሜ1 እና ድምዳሜ2፦ መጽሐፍ ቅዱስ የማይመዘን መመዘኛ ነው። ይህ ማለት ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ማለት ነው። አንተም ስትጠይቅ እኛ የምንለውን መጽሐፍ ቅዱስ ባለሥልጣን ነው ስንል ሌሎች ባለስልጣናንነታቸውን መካድ ማለት አይደለም። ይልቅ የማይመዘነው ብቸኛ የማይሳሳት መመዘኛ መጽሐፍ ቅዱስ ነው ማለት ነው። መልስ፦ እሺ። አሁን የእኛን እሳብ ተረዳህ? ጥያቄ፦ ይቀጥላል… ማጣቀሻ Augustine, Letter 19 (To Gaius):

መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን እንጠያየቅ – ክፍል 1 Read More »

ሥነ አመክንዮአዊ ተቃርኖ በመጽሐፍ ቅዱስ አይሳሳቴነት – ክፍል 2

ለዘብተኛ ምሑራን ሆኑ ከክርስትና ውጪ ባሉ ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስ ህጸጽ አልቦነትን በዚህ መልኩ ሲቃወሙ እናያለን፦መንደርደሪያ አንድ፦ በእጆቻችን ላይ ህጸጽ አልቦ የሆኑ እደ ክታባት የሉንምመንደርደሪያ ሁለት፦ እደ ክታባት ቅዱሳት መጻሕፍት ናቸው[¹]ስለዚህ: መጽሐፍ ቅዱስ ህጸጽ አልባ አፊዎተ ቃለ እግዚአብሔር አይደለም።(ማሳሰቢያ የሁለተኛው አዋጅ አጽዕኖት ከክርስቲያናዊ እደ ክታባት ያፈነገጠ ተደርጎ እንዳይታሰብ) በመጀመሪያ ይሄን ሙግት ርዕቱ ነው ወይስ አይደለም? ከማለታችን በፊት ህጸጽ አልቦነትን(inerrancy) ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት። ህጸጽ አልቦነትን ማለት ከስህተት የጸዳ እውነት አዘል አልያም ዝንፈተ እውነት የሌለበት ማለት ነው። አንዳንዶች የመጽሐፍ ቅዱስን ህጸጽ አልቦ አፊዎተ ቃለ እግዚአብሔርነቱ ላይ ሒስ ለማቅረብ ሲሉ ሁለት መሰረታዊ ነባቤ ቃላትን እርስ በእርሳቸው ያጠረማምሳሉ(ለምሳሌ የኤቲስቱ ባርት ኧርማን ሙግት)፤ ይኸውም የቃል በቃል አጠባበቅ እና ህጸጽ አልቦነትን ነው። ሁለቱ መሠረታዊ ልዩነቶች ያሏቸው ሲሆኑ የአንድ ነገር ንግግር ወይም ጽሑፍ የቃል በቃል አጠባበቅ ላይ ችግር ማግኘታችን ህጸጽ አልቦነቱን ላያሳጣው ይችላል። ባጭሩ የዚህ ሙግት ችግር የመጽሐፍ ቅዱስ እውነተኛ ግልጠት ማለታችን በእደ ክታቦቹ የቃል በቃል መስማማት አለባቸው ከሚለው ቅድመ ግንዛቤ ላይ የተመረኮዘ አለመሆኑን ካለመረዳት አንጻር ሊታይ ይችላል። ለምሳሌ ያክል የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በጻፈው ደብዳቤ በሁለት የግሪክ ቃላት ብቻ ልዩነት የተፈጠረ አንድ የሚስተዋል ልዩ ምንባባት አሉ፦ እንግዲህ በእምነት ከጸደቅን በእግዚአብሔር ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እንያዝ፤ሮሜ 5፥1 አንዳንድ እደ ክታባት ሰላምን እንያዝ የሚለውን ሐረግ ሲያካትቱ አንዳዶቹ ደግሞ ሰላም አለን የሚልን ነባቤ ሐረግ ይጠቀማሉ(አዲሱ መደበኛ ትርጉም በዚሁ መልክ ሲጠቀም ይታያል)። የግሪኩ ቃል አንዱ ኤኾሜን በኦሜጋ ፊደል(ἔχωμεν) ሲጠቀም ሌላኛው ደግሞ ኤኾሜን በኦሚክሮን ፊደል (ἔχὸμεν) ይጠቀማል። ምንም እንኳን እንደዚህ አይነት የቃላት ልዩነት ቢኖርም የአረፍተ ነገሩ ዋና ሐተታዊ እውነታው የሚደበዝዝ ወይም ሊናድ አይችልም። የአረፍተ ነገሩ ትክክለኛው አቀማመጥ፦ “peace is the possession of those who have been justified” እስከሆነ ድረስ የክታቡን ህጸጽ አልቦነት በቃላት ቦታ መለዋወጥ ሆነ አለመመሳሰል ልናጣው በፍጹም አንችልም። ምክንያቱም ህጸጽ አልቦነት የሚገናኘው ከትክክለኛ ዓርፍተ ሐሳቦ ጋር ነው። ነገር ግን አንድ መታወቅ ያለበት ነገር ቢኖር አንዳንድ የእደ ክታባቱ ልዩ መሆን(texual variant) ችግር ሆነው የሚመጡበት ጊዜ ሆነው የሚመጡበት ሰዓት ሊኖር ይችላል። ይሄን መሠል ችግሮች አገኘን ማለት ግን እንደነዚህ አይነቱን ለመለየት አስቸጋሪ አይደለም እንደውም በቀላሉ የሚለዩ ናቸው። ሙስሊሞችም ሆኑ ለዘብተኛ ምሑራን የሚጠቅሷቸው ነጠሮች በአጥባቄው ምሑራኑ ዓለም ውስጥ መልስ ተሰጥቷቸው ያለፉ ናቸው። በምሳሌም እውቁ የምንባባዌ(ጽሑፋዊ) ሕያሴ ስኮላር ዋላስ 99 በመቶ በላይ የሚሆኑት በእነርሱ መካከል ልዩ ምንባባት እንደሌሉ ይናገራሉ። Matthew Barrett በመጽሐፉ እንዲህ ሲል ያስቀምጠዋል፦ “….textual variations in the copies do not imply that the original manuscripts contained errors. These variations are seen as part of the natural process of transmission over time, but they do not undermine the truthfulness of Scripture as it was originally given. the existence of textual variants should not shake one’s confidence in the inerrancy of the Bible, as the original text remains reliable and intact, even if minor discrepancies exist in the copies..” በዚህ መሠረት ደግሞ በመጀመሪያው ጽሑፍ መካከል ልዩነት አለና በኋላ ላይ ባሉት ኮፒዎች ልዩነት አለ በሚሉ ሰዎች ሙግት ልዩነቶቹ በራሷቸው የእግዚአብሔር ቃል ህጸጽ አልቦ መሆኑን ሊሸፍኑ አንዳች አይቻላቸውም በማለት ክታባቱን ያጠኑ ምሑራን በዚህ መልክ ያስቀምጡታል ማለት ነው። ማጣቀሻ Barrett, Matthew. God’s Word Alone: The Authority of Scripture. Zondervan, 2016

ሥነ አመክንዮአዊ ተቃርኖ በመጽሐፍ ቅዱስ አይሳሳቴነት – ክፍል 2 Read More »

Scroll to Top