Islam

ዚኢዚሱስ ክርስቶስ አምላክነት

ክፍል 1 “እርሱ በባሕርዩ አምላክ ሆኖ ሳለ፣ ኚእግዚአብሔር ጋር መተካኚልን ሊለቀው እንደማይገባ አድርጎ አልቈጠሚውምፀ”  — ፊልጵስዩስ 2፥6 (አዲሱ መ.ት) አንድ አካል አምላክ ነው ዚሚባለው ወይም እንደ አምላክ ሊመለክ ዚሚገባው አምላክ ነኝ ብሎ ስለተናገሚ ብቻ ወይም ብዙዎቜ አምላክነቱን ስላወጁለት አይደለም። በመጜሐፍ ቅዱስ ላይ አምላክ ነኝ ብለው ዚተነሱ ነገሥታትን እንመለኚታለን። ለምሳሌፊ ዚጢሮስ ንጉስ እኔ አምላክ ነኝ ማለቱን(ሕዝቅኀል 28፥2-9) ስንመለኚት ይህ ንጉሥ እኔ አምላክ ነኝ ስላወጀ ብቻ አምላክ ነው ብሎ መፈሹጅ ፈጜሞ አይቻልም። በሰውም አጀብ አንድ አካል አምላክ ስለተባለም አምላክ ሊሆን አይቜልም። ምክንያቱም ዚግሪክ ጣዖታት እንዲሁ ተብለው ምንነታዊ ለውጥ ስላላሳዩን። ክርስቶስ ኢዚሱስ አምላክ ለመሆኑ ዚአምላክነት ግብሩንፀ ባህሪዎቱንና ሐልዎቱን በተለያዚ መንገድ መጜሐፍ ቅዱስ ሲናገርፀ ኑባሬውን ሲተርክና ሲገልጜልን እንመለኚተዋለን። ኚእነዚህም ዚመጜሐፍ ቅዱስ ክፍሎቜ ውስጥ አንደኛው ዚፊልጵስዩስ መልእክት ም2 ቁ6-7 ነው፩ ⁶ እርሱ በባሕርዩ አምላክ ሆኖ ሳለ፣ ኚእግዚአብሔር ጋር መተካኚልን ሊለቀው እንደማይገባ አድርጎ አልቈጠሚውምፀ ⁷ ነገር ግን ዚባሪያን መልክ ይዞ፣ በሰውም አምሳል ተገኝቶ፣ ራሱን ባዶ አደሹገ” ፊልጵስዩስ 2 (አዲሱ መ.ት) ᜃς ጐΜ Όορφῇ ΞεοῊ ᜑπάρχωΜ οᜐχ ጁρπαγΌ᜞Μ ጡγήσατο τ᜞ εጶΜαι ጎσα Ξεῷ, Προς Ίιλιππησιους 2:6 በጜርዑ ሞርፌ/Όορφῇ ዹሚለው ቃል ኑባሬያዊ መገኘትን፣ ሁናቮን ወይም ባህሪዎተ መልክን ዚሚገልጜ ቃል ሲሆን ክርስቶስ ኢዚሱስ (ወልድ) እም ቅድመ አለም በኑባሬው በባህሪዎተ መልኩ ራሱ አምላክ ሆኖ ዹሚኖር አካል እንደሆነ ይገልጻል። በተጚማሪም በባለቀትነት ሙያ (Nominative case) ዚመጣው ሁፓርኟን/ᜑπάρχωΜ ዹሚለው ቃል በአሁን ጊዜ አመልካቜ ግስ(Present participle tense) መምጣቱ ወልድ ኹዘላለም ጀምሮ ኚአብ ጋር አብሮ ህያው አብሮ እኩል አብሮ ዘላለማዊ እንደሆነ በሚገልጜ መልኩ እንደመጣ ዹክፍሉን ሰዋሰው ይነግሚናል። ይህም ደግሞ ለወልድ ኑባሬ ጅማሮ አለው ፍጡር እንጂ ፈጣሪ አይደለም ለሚሉት አርዮሳውያን እና ኢብዮናውያን (Ebionite/ጘβιωΜαῖοι) በተለምዶው አዶፕሜኒስቶቜ ዚሚባሉት ዹምን*ፍቅና ዚአስተምህሮቶቜን መሰሚታ቞ውን ዚሚንድ ክፍል ነው። ሙግታቜንን ጠበቅ ለማድሚግ ያክል ኚተመለኚትን ደግሞ ወልድ አምላካዊ ባህሪ ኚጥንተ ዘላለም ጀምሮ በዚሁ መልክ ሲኖር ዹነበሹው አምላክ ወደ ፈጠራት ጠባበ አለም ዹሰውን ወይም ዚባሪያን ባህሪ(መልክ) ይዞ መምጣቱ “ኚእግዚአብሔር አብ ጋር መተካኚልን ሊለቀው እንደማይገባ አድርጎ አልቈጠሹውም” በማለት ብርሃነ አለም ቅዱስ ጳውሎስ ፍንትው አድርጎ ዚወልድን መለኮታዊ ባህሪዎት ኚእግዚአብሔር አብ ጋር እኩል እንደሆነ ያሳዚናል። ኹአምላክ ጋር እኩል መሆን ወይም በጜርዑ ቶ ኢናይ ኢሳ ቮኩ/τ᜞ εጶΜαι ጎσα Ξεῷ ዹሚለው ሐሹግ እግዚአብሔር ወልድ ኚእግዚአብሔር አብ ጋር በባህሪው እኩል ወይም አንድ አይነት ሆሙስዮስ/ᜁΌοούσιος እንደሆነ በግልጜ ሁኔታ ሲነግሚን ዚአርዮሳውያንን መርሆተ ቃል ዹሆነውን ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ባህሪዎት ሆሞዮስዮስ/ᜁΌοιούσιος ዹሚለውን ምንፍቅና አፈር ኚመሬት ዚሚደባልቅ ክፍል እንደሆነ እንመለኚታለን። በቁጥር ሰባትን አንድ በአንድ ስንመለኚተው “ዚባሪያን መልክ ይዞ” ዹሚለው ሐሹግ በፊት ዚተገለጠበት ቅድመ ኑባሬያዊ ባህሪዎት እንደነበሚው ቁልጭ አድርጎ ያሳዚናልፀ እርሱም በቁጥር 6 ላይ እንዳዚነው ዚወልድ አምላካዊ መልክ (ባህሪ) ኚጥንተ ዘላለም ጀምሮ ገንዘቡ ዹሆነ ምንነት ነው። “በሰውም ምሳሌ ሆኖ” ዹሚለው አገላለጜ ደሞ ወደ ምድር በመጣ ጊዜ ፈጣሪ በፍጡራን ምሳሌ ሆኖ ሰዋዊ ባህሪዎትን እንደተላበሰ ያሳዚናል። ቀጥሎም “ራሱን ባዶ አደሹገ” ዹሚለው ደሞ አንድ ነገር ባዶ ሆነ ዚሚባለው ያ ነገር መጀመሪያውኑ ዹሆነ ነገር ሲኖሚው ነው። ክርስቶስ ኢዚሱስ ደግሞ ራሱን ባዶ አደሹገ ሲባል አምላካዊ ሙሉነት ዹነበሹው አካል ወደ ፈጠሚው፣ ወዳዘጋጀው፣ ሰዋዊ ባህሪዎት ዝቅ ብሎ በመምጣቱ ነው። ስለዚህ ክርስቶስ ኢዚሱስ ሰው ሁኖ ኚመምጣቱ በፊት በአምላካዊ ሙሉነት ዹሚኖር አምጻኀ ኩሉ አምላክ እንደሆነ እንመለኚታለን። በመጚሚሻም ዚክርስቶስን አምላክነት ዚማያምኑ እንዲህ ሲሉፊ” ክርስቶስ ኢዚሱስ (ወልድ) በእግዚአብሔር ወይም በአምላክ መልክ መኖሩ አዳም በእግዚአብሔር መአልክና ምሳሌ በተፈጠሚበት ሒሳብና ቀመር ነው
” ይሞግታሉ። ነገር ግን ዚሁለቱን ክፍሎቜ ዚጜርዑን ዚቃላት አገባብ እና አውዳዊ ምልኚታ ባደሚግን ጊዜ ፈጜመው ዹዹቅል ሐሳብ እንደሆነ እንሚዳለንፊ እግዚአብሔርም አለ፩ ሰውን በመልካቜን እንደ ምሳሌአቜን እንፍጠር/κα᜶ εጶπεΜ ᜁ Ξεός ΠοιήσωΌεΜ ጄΜΞρωποΜ κατៜ εጰκόΜα ጡΌετέραΜ κα᜶ καΞៜ ᜁΌοίωσιΜ >>  — ዘፍጥሚት 1፥26 በዘፍጥሚት 1፥26 መልክ ብሎ ዚገባው ዚግሪኩ ቃል ኀይኮና/εጰκόΜα ሲሆን ምሳሌ ዹሚለው ደሞ ሆሞዮሲን/ᜁΌοίωσιΜ በሚለው ዚቃላት አገባብ እንደተሰደሚ እንመለኚታለን። ኀይኮና/εጰκόΜα ዹሚለው ቃል ኀይኮን/εጰκ᜜Μ ማለትም ምስለ መልክን መመሳሰል ወይም መቀራሚብ(በውጫዊ ማንነት መገለጫ) ዹሚል ትርጉም አለው። እግዚአብሔር አምላክ ሰውን በእኛ መልክ(ኀይኮና ሄሜ቎ራን/εጰκόΜα ጡΌετέραΜ) እንፍጠር ሲል በጜድቅና ቅድስና(ኀር 4:24)ፀ እንዲሁም በመገንዘብ ቜሎታንና እውቀትን(ቆላ 3:10) ዚመሳሰሉትን ዚምስስሎሜ መገለጫዎቜ በሚገልጜ አገባብና አግባብ መምጣቱ ቅብል ነው። ነገር ግን ዹሰው ልጅ በእግዚአብሔር መልክና አምሳል መፈጠሩ በእርግጥ ዚሚካፈለው ባህሪ እንዳለው ሁሉ ዚማይካፈለው ባህሪ አለ። በዛው በፊልጵስዩስ መልእክት 1:7 እና 2ኛ ጎጥሮስ 1፥4 ላይ ዚእግዚአብሔር ዚባህሪው ተካፋዮቜ እንደሆንን ይናገራልፊ “ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣቜሁ ኚመለኮት ባሕርይ ተካፋዮቜ(κοιΜωΜο᜶ φύσεως) በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት ዹተኹበሹና እጅግ ታላቅ ዹሆነ ተስፋን ሰጠን።”2ኛ ጎጥሮስ 1፥4 ተካፋይ ወይም በግሪኩ ኮይኖኖስ/κοιΜωΜ᜹ς ዹሚለው ቃል ዹሰው ልጅ ኚእግዚአብሔር ፈጜሞ ዚማይካፈለው ወይም ዚቀሚበት ነገር እንዳለ አመላካቜ ነው። ይህንን ሐሳብ በሌላ ክፍል በስፋት እንመለኚተዋለን። ነገር ግን ክርስቶስ ኢዚሱስ ኚእግዚአብሔር አብ ጋር ዚማይጋራው ሆነ ዚማይካፈለው ባህሪ ዚለም። ኹላይ በፊልጵስዩስ መልእክት 2:6 ኚአብ ጋር በመለኮተ ባህሪዎት እኩል ወይም አንድ እንደሆነ ተመልክተናል። ስለዚህ አምላክ ክርስቶስ ኢዚሱስ በአምሳለ ሰውነት መገለጡ (እንደ ሰው መብላት መጠጣቱፀ መተኛት መነሳቱፀ መወለድ ማደጉ ወዘተ) መለኮታዊ ክብር እንደሌለው ዚሚያሳዚን ተግባር አይደለም። እርሱ ወደዚቜ ወደ ፈጠራት አለምና ሰውነት ኚመገለጡ በፊት አምላካዊ ምንነትፀ ክብርና መለኮታዊ ኑባሬ ኚጥንተ ዘላለም ጀምሮ ገንዘቡ ያደሚገ ኃያል አምላክ ነው።

ዚኢዚሱስ ክርስቶስ አምላክነት Read More »

ዚኒቂያ ጉባኀ እና ጥንታዊያን አበው

ለሙስሊም ሰባክያን ሙግት ምላሜ ሰሞኑን በሙስሊሞቜ ዘንድ በማህበራዊ ሚዲያ ሲሰራጩ ኚነበሩ ሙግቶቜ መካኚል አንዱ ተኚታዩ አንድ ሙስሊም ዚጻፈው ጜሑፍ ነው። ዹዚህ ጜሑፍ አዘጋጅ ዚዕውቀቱ ልክ በጜሑፎቹ ውስጥ ዚሚታዚው ኹሆነ ራሱን ዚማስተማር ብቃት እንዳለው ሰው በመቁጠር ለመጻፍ መድፈሩፀ አንባቢያኑም ደግሞ ይህንን ሙግት ኹቁም ነገር ቆጥሚው መቀበላቾው ዚሚያሳዝን ነው። ሙግቱም እንዲህ ሲል ይጀምራልፊ አብዱል በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 112፥3 «አልወለደም አልተወለደምም»፡፡ ጥንት ላይ ዚነበሩ ነቢያት እንዲሁ ኢዚሱስ እና ሐዋርያት አሓዳዊያን”Unitarian” ዚነበሩ ሲሆን ኚሐዋርያት ኅልፈት በኃላ ዚተነሱ ዚቀተክርስቲያን አበው ደግሞ በሂደት “ክልዔታውያን”Binitarian” ነበሩ። ኚክልዔታውያን አበው መካኚል ጠርጡሊያኖስ”Tertullian” ስለ ወልድ ሲናገር እንዲህ ይለናል፩ “አብ አጠቃላይ ባሕርይ ነው፥ ነገር ግን ወልድ ዚአጠቃላዩ መገኘት እና ክፍል ነው” (Against Praxeas (Tertullian), Chapter 9) መልስ ዚብሉይ ኪዳንን ቅዱሳት መጜሐፍት ስንመለኚት እግዚአብሔር አምላክ ነጠላ አንድ ነበሹ ማለት አንቜልም። ለዚህም ማሳያ መጜሐፍ ቅዱስ በዘፍጥሚት 1፥26 እንዲህ ይላልና፩ “እግዚአብሔርም አለ፩ ሰውን በመልካቜን እንደ ምሳሌአቜን እንፍጠርፀ ዚባሕር ዓሊቜንና ዹሰማይ ወፎቜን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ ዚሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።” á‹šáŠ¥áŒá‹šáŠ á‰¥áˆ”áˆ­áŠ• ሥሉስ አሓዳዊነት ኚሚያመለክቱ ዚመጜሐፍ ቅዱስ ክፍሎቜ መካኚል አንዱ ኹላይ ያነበብነው ጥቅስ ነው። እግዚአብሔር አብ ዓለማትን በልጁ መፍጠሩን (ዕብ1፥2ፀ ዮሐ1፥3ፀ ቆላ1፥16-17) እንዲሁም ደግሞ ፍጥሚትን በማስገኘት ሒደት ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ጉልሕ አስተዋጜኊ እንደነበሚው ቅዱሳት መጻሕፍት አበክሹው ይነግሩናል (ዘፍ 1፥3 ፀ ኢዮ33፥4)። በዘፍጥሚት 1፥26 ላይም በብዙ ቁጥር ግስ “እንፍጠር” (נַעֲשֶׂה “ናዓሮህ”)፣ በብዙ ቁጥር ስሞቜ “በመልካቜን” (בְ֌׊ַלְמֵ֖נו֌ “ቀጻልሜኑ”) እንዲሁም “ምሳሌአቜን” ( כ֎֌דְמו֌תֵנו֌ ”ኪድሙ቎ኑ”) ማለቱ አሐዱ ሥሉስን እንደሚያመለክት በርካታ ዚመጜሐፍ ቅዱስ ምሑራን ዚሚስማሙበት እውነታ ነው፡፡ በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ በገጻቜን ዚጻፍነው ጜሑፍ መመልኚት ይቻላል።[1] á‹­áˆ… ሙስሊም ጾሐፊ ቀጠል አድርጎ ዚቀተክርስቲያን አበው ሥላሎያውን አልነበሩም ብሎ በድፍሚት ይናገራል። ነገር ግን ይህ ፍጹም ሐሰት እና ቅጥፈት ነው። ይባስ ብሎ áŒ áˆ­áŒ¡áˆŠá‹«áŠ–áˆµáŠ•áˆ ጚምሮ á‹šáŒ¥áŠ•á‰µ ቀተክርስቲያን አባቶቜ “Binitarian” ናቾው ይለናል። በዚህ ንግግሩ ጾሐፊው ዚቀተክርስቲያን ታሪክ እውቀት ዹለውም ወይም ደግሞ ሆነ ብሎ አንባቢያኑን እዚዋሞ ነው ማለት ነው። ሙስሊሙ ወገናቜን ላነሳው ሀሳብ ምላሜ ኚመስጠታቜን በፊት በትምህርተ ሥላሎ ላይ ዚቀተ-ክርስቲያን አበው ዚነበራ቞ው አቋም ጥርት ያለ እንደነበር እስኪ በጥቂቱ እንመልኚትፊ 1) ፖሊካርፕ (Polycarp):- በ70ዓ.ም ተወልዶ በ155 ዓ.ም ወይም በ160 ዓ.ም ዚሞተ፣ ዚሐዋሪያው ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ዹነበሹ ሲሆን ዚሰምርኔስ ቀተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዹነበሹ ሰው ነው። ትምህርተ ሥላሎን በተመለኹተ እንዲህ ይላል፩ ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር ሆይ
ዘላለማዊና ሰማያዊ በሆነ ሊቀ ካህናት፣ በምትወደውና ባኚበርኞው ልጅህ በኢዚሱስ ክርስቶስ በኩል ለአንተና ለእርሱም እንዲሁም ለመንፈስ ቅዱስ አሁንም ሆነ ለዘላለም ክብር ይሁን[2] 2) ዮስጢኖስ ሰማዕት(Justin Martyr) ፊ በቀተክርስቲያን ዚእምነት ተሟጋቜና አቃቀ እምነት ዹነበሹው ይህ አባት በ100 ዓ.ም ተወልዶ በ165 ዓ.ም እንደሞተ ይገመታል። ይህ አባት በአቅብተ እምነት ጜሑፉ ላይ ትምህርተ ሥላሎን በተመለኹተ እንዲህ በማለት ጜፏልፊ ዚዓለማት ጌታ በሆነው በእግዚአብሔር አብ፣ በመድሐኒታቜንም ኢዚሱስ ክርስቶስ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ ስም በውሃ መታጠብን ያገኛሉ።[3] 3) አግናጢዮስ ዘአንጟኪያ(Ignatius of Antioch) ፊ ዚአንጟኪያ ቀተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዹነበሹና ኹ98 ዓ.ም እስኚ 117 ዓ.ም መካኚል ሰማዕት እንደሆነ ዚሚነገርለት አባት ክርስትናን ኹመናፍቃን በመኹላኹሉ ዙሪያ ብዙ ዚጻፈ ዐቃቀ ክርስትና ነው። ትምህርተ ሥላሎን በተመለኹተ እንዲህ በማለት ጜፏልፊ በጌታቜንና በሐዋርያት ትምህርት እድትጞኑ፣ á‹šáˆá‰³á‹°áˆ­áŒ‰á‰µ ነገር ሁሉ በስጋና በመንፈስ እንዲኚናወንላቜሁ፣ á‰ áŠ¥áˆáŠá‰µáŠ“ በፍቅርፀ በወልድ፣ በአብና በመንፈስ ቅዱስ፣ á‰ áˆ˜áŒ€áˆ˜áˆªá‹«á‹ እና በመጚሚሻውፀ ኹተወደደው ጳጳሳቜሁ፣ በጎ ኹሆነው ዚሜማግሌአቜሁ መንፈሳዊ አክሊል፣  áŠ¥áŠ“áˆ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ካሉ ዲያቆናት ጋር አጥኑ። á‰ áˆµáŒ‹á‰œáˆáˆ በመንፈሳቜሁም አንድነት እንዲኖራቜሁ áŠ­áˆ­áˆµá‰¶áˆµ ኢዚሱስ ለአብ በስጋው እንደተገዛለት፣ ሐዋርያት ለክርስቶስ ለአብ እና ለመንፈስ ቅዱስ እንደተገዙ፣ እናንተም ለጳጳሳቜሁ እና እርስ በእርሳቜሁ ተገዙ(ታዘዙ)። [4] 4) ጠርጡሊያኖስ ወይም ተርቱሊያን (Tertullian 160-215) አፍሪካዊ ዕቃቀ ክርስትና እንዲሁም ዹነገሹ መለኮት ሊቅ ነው። ዚጥንቷ ቀተ ክርስቲያን አባት ዹሆነው ጠርጡሊያኖስ በሥላሎያዊ አስተምህሮ ላይ ለሚነሱ ኑፋቄዎቜ መልስ በመስጠትና በክርስቲያናዊ ሥነ-መለኮት ኚሚሰሩ አቃብያነ አባቶቜ መካኚል አንዱ ነው። ለምሳሌ በመናፍቃን ሙግት ላይ ባነሳው በፕራክሲዚስ (against praxeas) ዚሞዳሊዝም አራማጅ ዹሆነው ዚፓትሪፓሺያን(Patripassian) ሐሳብ አንስቶ እንዲህ ሲል በሙግቱ ላይ ጜፏል፡- ሶስቱ አብ፣ ወልድና መንፈሱ ና቞ው። ሶስት ና቞ው። ነገር ግን በሁናቮ አይደለም በግብር እንጂፀ በኑባሬም አይደለም በአካል እንጂፀ በስልጣን ወይም በሐይል አይደለም በገጜታ እንጂ ሆኖም ግን እግዚአብሔር አምላክ አንድ ኑባሬ፣ ስልጣን፣ ሐይል አለው ምክንያቱም በአካል፣ በግብርና በአይነት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ዹተገለጠ አንድ አምላክ ነውና..[5] እንግዲህ ጠርጡሊያኖስ እና ሌሎቜ በርካታ አበው አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ኹዘላለም ያለመሜቀዳደም እንዲሁም ያለመነጣጠል አሐዱ ሥሉስ እንደነበሩ ይነግሩናል። እንደ ሮሙ ቀለሜንጊስ(30-95)፣ ሔሬኒዚስ (115-190) እና ቀጰዶቃውያን አበው (Cappadocian Fathers) ያሉ ዚቂሳርያው ትልቁ አባት ባስልዮስ፣ ጎርጎርዮስ ዘንዚናዙ፣ ጎርጎሪዮስ ዘኑሲስ እንዲሁም ሌሎቜ ዚቀተክርስቲያን አባቶቜ እንዘርዝር ብንል ትምህርተ ሥላሎን በተመለኹተ በድርሳና቞ው ዚጻፉትን áŠ¥áˆá መሹጃ áŠ¥áŠ“áŒˆáŠ›áˆˆáŠ•á¢ ስለዚህ ሙስሊሙ ጾሐፊ â€œá‹šá‰€á‰°áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ• አባቶቜ ስለ ሥላሎ ግንዛቀ ዹላቾውም ይልቅ አብና ወልድን ብቻ ጠቅሰው መንፈስ ቅዱስ ህልውና ዹለውም ብለዋል” á‰ áˆ›áˆˆá‰µ â€œáŠ­áˆá‹”á‰³á‹á‹«áŠ• “Binitarian” ነበሩ” á‰ áˆ›áˆˆá‰µ á‰ áŒœáˆ‘ፉ ያሰፈሚው ፈጜሞ ኚእውነት ዚራቀ ነው። ይህን መሠል ሙግት ደሞ ኹላይ ባስቀመጥና቞ው ዚአባቶቜ ትምህርት ውድቅ ይሆናል። በመቀጠል ይህ ሙስሊም ጾሐፊ ሙግቮን ይደግፋል በማለት ዚአርዮሳውያንን ሙግት በመውሰድ ለመሞገት ሲጣደፍ ይስተዋላል። ሙስሊሙ ጾሐፊ ይህንን ሀሳቡን ለመደገፍ ዹጠቀሰው ዚጠርጡሊያኖስ ሥራ ኹሆነው “Against Praxeas” ኹተሰኘው ጜሁፍ ነው። ይህ አባት በጜሑፉም ሆነ በቃል ዚሥላሎን ትምህርት እውነተኝነት እዚተሟገተ እና ዚሞዳሊዝምን (አብ፣ ወልድ እና መንፈስ አንድ ነጠላ አካል ነው áˆˆáˆšáˆ‰) á‰µáˆáˆ…ርት አቀንቃኝ áˆ˜áŠ“áá‰ƒáŠ• እዚሞገተ ዚጻፈው ጜሁፍ ነው። በዚህ ዐውደ-ጜሑፍ ጠርጡሊያኖስ ዚሚኚራኚሚው በሊስት አካል ስለተገለጠው አንዱ መለኮት ነው። በምዕራፍ 9 ሙሉ አውዱ እንዲህ ሲል ይጜፋልፊ “Bear always in mind that this is the rule of faith which I profess; by it, I testify that the Father, and the Son, and the Spirit are inseparable from each other, and so will you know in what sense this is said. Now, observe, my assertion is that the Father is one, and the Son one, and the Spirit one, and that They are distinct from Each Other. This statement is taken in a wrong sense by every uneducated as well as every perversely disposed person, as if it predicated a diversity, in such a sense as to imply a separation among the Father, and the Son, and the Spirit.” “እኔ ዹምመሰክሹው ዚእምነት መርህ ይህ መሆኑን ልብ በሉ። በዚህም አብ፣  á‹ˆáˆá‹µáŠ“ መንፈስም ዚማይነጣጠሉ እንደ ሆኑ እመሰክራለሁ። ነገር ግን በምን መንገድ ይህ እንደሚባል áŠ áˆµá‰°á‹áˆ‰á¢  እንግዲህ ዹኔ ሙግት “አብ አንድ እንደ ሆነ፣ ወልድም አንድ እንደሆነ፣ መንፈስም አንድ እንደ ሆነፀ ነገር ግን እርስ በርሳ቞ውም ልዩ (distinct) እንደ ሆኑ ነው። ይሄም አገላለጜ ባልተማሚ ሁሉ እንዲሁም ጠማማ አስተሳሰብ ባላ቞ው ሰዎቜ ሁሉ በተሳሳተ መንገድ ይወሰዳል። በአካላቱ[በአብ፣ በወልድ እና በመንፈስ] መካኚል መለያዚትን እንዳለብ በሚያመለክት መልኩ ብሎም በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ መካኚል  áˆ˜áŠáŒ£áŒ áˆ እንዳለ በማሳዚት አጣምመው ይተሚጉማሉ።[6] ሙስሊሙ ጾሐፊም ኹላይ ጠቅሶ ዚጻፈው በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ዹተጠቀሰ ሲሆን። ኚአውዱ ውጭ ገንጥሎ በማውጣት ለአንባቢያኑ ጜፎላ቞ዋል። ዚጠርጡሊያኖስ ጜሁፍ እንዲህ ይነበባልፊ “Thus the Father is distinct from the Son, being greater than the Son, in as much as He who begets is one, and He who is begotten is another; He, too, who sends is one, and He who is sent is another; and He, again, who makes is one, and He through whom the thing is made is another

..Lord

ዚኒቂያ ጉባኀ እና ጥንታዊያን አበው Read More »

ሑባል(هؚل)

እስልምና እና ዚአሚቡ ጣዖታት ክፍል 1 እንደሚታወቀው እስልምና ሲነሳ በአእምሯቜን ፈጥኖ ዚሚሳለው ዚገሚሱ ጹሹቃ እና ኮኚብ አርማ ነው። በትላልቅ መስጂዶቜ አናት ላይ በሚናራዎቜ[¹] እንዲሁም እስላማዊ በሆኑ ኪነ ህንጻዎቜ ላይ ዚሚስተዋል ምልክት ነው። በሰባተኛው መቶ ክ/ዘ መጀመሪያዎቹ አካባቢ ዚእስላማዊ አገሮቜ መገበያያ ዹጹሹቃ እና ኮኚብ ምስል ያለው ሳንቲሞቜን እንደሚጠቀሙ አርኪዎሎጂስቶቜ ያትታሉ።[²] በ11ኛው መቶ ክ/ዘ ግብጻውያን እና ሶርያውያን ይህንን ምልክት ለጌጣጌጣ቞ው ማስዋቢያነትም ይጠቀሙት ነበር።[³] በተጚማሪም አንዳንድ አገራት ማለትም እንደ አልጀሪያ፣ አዘርባጃን፣ ኮሞሮስ፣ ማሌዥያ፣ ሞሪታንያ፣ ፓኪስታን፣ ቱኒዚያ፣ ቱርክ፣ ዚቱርክ ሪፐብሊኳ ሰሜኒቷ ቆጵሮስ፣ ኡዝቀክስታ ዚምዕራብ ሰሐራ 
ወዘተ  እስላማዊ አገራት ይህንኑ አርማ እንደ ሀገራዊ መለያ ሰንደቅ ማድሚጋ቞ው ይታወቃል።[⁎] እስልምና ኹጹሹቃ እና ኮኚብ ምልክት ጋር ምን ግንኙነት አለው? ይህንን ግንኙነት ለመሚዳት ዲነል ኢስላም ኚመጀመሩ በፊት ጥቂት አመታት እልፍ ብለን ስንመለኚት በመካ ይመለኩ ኚነበሩ ጣዖታት መካኚል አንዱ ሑባል(هؚل)  ዹጹሹቃ እና ዚኚዋክብት አምላክ እንደነበር ዚታሪክ መዛግብት ያትታሉ።[⁵] ሑባል(هؚل) ዹአሏህ ቀት ተብሎ በሚጠራው በካዕባ ውስጥ ትልቅ ስፍራ ዹነበሹው እና ለነገደ አሚቡ ጣዖት አምላኪያን ሐያል አምላክ እና ታላቁ ጣዖታ቞ውም ነበር።[⁶] ዚሑባል ሌላኛው ስሙ “ሏህ” በመባል ይታወቅ ነበር። እንደ ሮበርት ሞሪ ያሉ ስኮላሮቜ ጥናት መሠሚት ኚአርኪዎሎጂስቱ ተመራማሪ ሁጎ ዊንክለር ጥናት በመነሳት “አሏህ” ዹሚለው ስም ለቅድመ እስላማዊ ዚአሚብ ማህበሚሰብ አፈታሪክ ውስጥ ለጹሹቃ አምላካ቞ው ስያሜ እንደዋለ ይነግሚናል።[⁷] ጁሊዚስ ዌልሃውሰንም ጚምሮ ዚእስልምና ሐይማኖት ኚማንሰራራቱ በፊት ዹአሏህ ቀት ተብሎ ዚሚጠራው ካዕባ በጣዖቱ ሑባል ሐውልቶቜ ቁሳቁሶቜና ስዕላት ተሞልቶ እንደነበርና ሑባል ዹአሏህ ዚመጀመሪያ ስሙም እንደነበር ይናገራል።[⁞] ነገር ግን በእስልምናውም ላሉ ሊቃውንቶቜ ሆነ ለለዘብተኛ ዚታሪክ አጥኝዎቜ ጥያቄ ዹሆነው ክስተት አሏህ ስለዚህ ታላቅ ዚአሚቊቜ ጣዖት በሐዲሱ ላይ አንድ ሱፍያን ኢብን ሀርብ ዚተባለ ዚቁሚይሜ ዹጩር መሪ ኚባድር ጊርነት በኋላ ድልን እንዲሰጣ቞ው እንደተጣራና ሑባልን እንዳመሰገነ[⁹] ኚመጥቀሱ ባለፈ በቁርአኑ ውስጥ በስሙ ተጠቅሶ አለመነሳቱ ነው። እንደ እነ አል ላት አል ኡዛ እና እንደ እነ አል መናት ያሉ ጣዖቶቜ በቁርአኑ ውስጥ ተጠቅሰው ሳሉ ጣዖቱ ሑባል አለመጠቀሱ አጠያያቂ ጉዳይ ነው። እንደ አንዳዶቜ አባባል ቁርአን በካዕባ ስለነበሩ ሶስት መቶ ስልሳ ጣዖቶቜ እያንዳንዱን ስም እዚጠቀሰ ግድ መናገር ዚለበትም ይላሉ። ነገር ግን ቁርአን በቁሚይሟቜ ነገድ እንደ ሑባል በገነነ መልኩ ዚማይመለኩትን በስም ጠቅሶ ኹገለጠ ስለ ሑባል አለማውራቱ አግራሞትን ዚሚያጭር ጉዳይ ሁኖ እናገኘዋለን። ይህ ዚሆነበት እንደምክንያት ዚሚነሳው ዚእስልምናው ሐይማኖት ቆርቋሪ እና መስራቜ ዹሆነው መሐመድ ኚጣዖቱ ሑባል ጋር ዚተቆራኘ ታሪክ ስላለው ነው። ነብይ ተብዬው ኚመወለዱ በፊት አያቱ አብዱል ሙጠሊብ ዚጣዖቱ ሑባል አምላኪ እንደነበር ዚእስልምና ታሪክ መዛግብት ይናገራሉ።[¹⁰] አብዱል ሙጠሊብ ኚልጆቹ መኻል እጣው ዚወደቀበትን ልጅ በአሁኑ ጊዜ ቅዱስ ስፍራ ተብሎ በሚጠራው በካዕባ ለጣዖት ሑባል መስዋዕት አድርጎ ለማቅሚብ በደጋን እጣ በልጆቹ ላይ ይጥላል። ዹደጋኑም ጫፍ ዚመሐመድ አባት በሆነው በአብደላህ ላይ ያመልክታል። ዚመሐመድም አያት ልጁን ለመሰዋት ማሹጃ እንዳነሳና ነገር ግን ቁሚይሟቜ፣ ኹመኾዙም ጎሳ ዹሆነው አጎቱ እና ወንድሙ ልጁን እንዳይሰዋ አሳምነው አብዱል ሙጠሊብ በመሐመድ አባት አብደሏህ ምትክ ዹሚሆን ዹግመል መስዋዕት ለሑባል እንዳቀሚበ እንመለኚታለን።[¹¹] እንደውም እንደ ጠበሪ ዘገባ አብዱል ሙጠሊብ መሐመድ ጹቅላ እንደነበር ወደ ጣዖቱ ሑባል ፊት ያመጣው እንደነበር ይተርካል።[¹²] ይህ ሁሉ ዚታሪክ ማስሚጃዎቜ ዚሚያሳዩን ዹቁርአኑ ደራሲ መሐመድ ኚሑባል ጣዖት ጋር ገና ኚመወለዱ ጀምሮ ህጻንም እያለ ጥብቅ ቁርኝት እንደነበሚው ያሳያል። ምንም እንኳን መሐመድ በካዕባ ዚሚገኙትን ዚሑባልን ጣዖት እና መገልገያዎቜን ለማጥፋት ቢሞክርም ዚሑባል ጣዖት ዚአምልኮ ስርአቶቜን ለምሳሌ በካዕባ ዙሪያ ጠዋፍ ማድሚግን(ዚቅድመ አሚባውያን ዚጣዖት አምላኪዎቜ ልምምድ ነበር ለጣዖት ሑባልም ይህንኑ ዚአምልኮ ስርአት አምላኪዎቹ ይኹውኑ ነበር) ዚጣዖቱ ስም ኚአምላኩ ስም ጋር ማመሳሰሉ(ቀደምት እስልምና ዚጣዖት አምላኪያውያን አምላካ቞ውን ላህ ወይም ሑባል በማለት ይጠሩት እንደነበር እና ዚእስልምናው አምላክ ስም ኚጣዖታውያኑ ጋር ጥልቅ ቁርኝት ነበሹው) በተጚማሪም ዹአሁኑ ዚሙስሊም  ማህበሚሰብ ዚሚጠቀምበት ዚእምነት መለያ አርማቾው ያደሚጉት በጥንቱ ዚአሚብ ጣዖት አምላኪያን ዘንድ ለሑባል ዹተሰጠ ዚጣዖታ቞ው መለያ መሆኑ ይህ ሁሉ ዚሚያሳዚን እስልም ዚቅድመ አያቶቹን ዚአሚብ ጣዖታውያንን ዚሐይማኖት ስርአት፣ ስያሜ ዚማምለኪያ ቊታ(ካዕባ) እና ዚመለያ ምልክቱን መኮሚጁ ወልደ ጣዖታውያን ዚእምነት መሠሚት መሆኑን በግልጜ ሁኔታ መሚዳት ዚምንቜለው ዚሐይማኖት ቡድን እንደሆነ ነው። መጜሐፍ ቅዱሳቜን ግን፩ “እኔ እግዚአብሔር አምላካቜሁ ነኝና ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ ዹተቀሹጾም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙፀ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራቜሁ ላይ ዹተቀሹጾ ድንጋይ አታኑሩ።”  — ዘሌዋውያን 26፥1 በማለት እንዳናመልክና እውነተኛውን ጌታ እንድንኚተል ያደርገናል። እግዚአብሔር በዚህ መንገድ ይመራ቞ው ዘንድ ፀለይን አሜን። ማጣቀሻዎቜ [¹] International Federation of Red Cross & Crescent Societies [²] S. Album & T. Goodwin – Syllogue Of Islamic Coins In The Ashmolean – The Pre-Reform Coinage Of The Early Islamic Period – 2002, Volume I, Ashmolean Museum: Oxford (UK), pp. 6-7 [³] “Pendant (Egypt) (30.95.37)”. In Heilbrunn Timeline of Art History. New York: The Metropolitan Museum of Art, 2000–. (October 2006) [⁎] Islamic flags – Flags Of The World, October 18, 2008 [⁵] Karen Armstrong (2000,2002). Islam: A Short History. pp. 11 [⁶] ዝኒ ኹማሁ [⁷] Morey, Robert(1994)The Moon-god Allah in Archeology of the Middle East. Newport, Research & Education Foundation. [⁞] Wellhausen, Julius. Reste Arabischen Heidenthum, pp. 75/ Hawting, Gerald R.(1999). The Idea of idolatry & the emergece of Islam: from polemic to History. pp. 112 [⁹] Winckler, Hugo(1901) Arabisch, Semitisch, Orientalisch: Kulturgeschichlich-Mythologische Untersuchung.Berlin:W. Peiser pp. 83 [¹⁰] Ibn Hisham 1/151-155; Rahmat-ul-lil’ alammeen 2/89, 90 [¹¹] ዝኒ ኹማሁ [¹²] Mohammed ibn Jarir al-Tabari, The History of the Prophet & Kings,1:157

ሑባል(هؚل) Read More »

ማርያም ዚሐሩን እህት?

“ዚእንበሚም(አምራም/עַמְך֞ם) ሚስት ስም ዮካብድ(ዮኬቬድ/יוֹכֶבֶד) ነበሚ። እርስዋ በግብፅ ኹሌዊ ዚተወለደቜ ዹሌዊ ልጅ ነበሚቜፀ ለእንበሚምም አሮንንና(አኻሮን/אַהֲךוֹן) ሙሮን(ሞሌኜ/מֹשֶׁה) እኅታ቞ውንም ማርያምን(ሚርያም/מ֮׹ְי־ם) ወለደቜለት።”— ዘኍልቁ 26፥59 በመጜሐፍ ቅዱሳቜን መሰሚት ዚአሮን (አኻሮን/אַהֲךוֹן)፣ ዹሙሮና(ሞሌኜ/מֹשֶׁה) ዚነብይቷ ማርያም(ሚርያም/מ֮׹ְי־ם) አባታ቞ው እንበሚም(አምራም/עַמְך֞ם) ነው።እንበሚም በእብራይስጡ አምራም/עַמְך֞ם በ ፊደል ሜም “ם” ሲያበቃ በአሹበኛው መጜሐፍ ቅዱስ ላይ አምራም(عمرام) በፊደል ሚም(م) ዚሚጚርስ ቃል ነው፩ أؚْناءُ عَمْرامَ هُمْ هارُونُ وَمُوسَى وَمَرْيَمُ ዚእንበሚምም ልጆቜ አሮን፥ ሙሎ፥ ማርያም።”— 1 ዜና 6፥3በቁርአኑ ላይ ደግሞ ኢምራን(عمران) በፊደል ኑን(ن) በሚያበቃ ስም ተጠቅሶ እናገኘዋለን[¹]። ذكر نسؚ موسى ØšÙ† عمران (ዚአት-አጠበሪ ታሪክ ቅጜ3) ቀዓት(ቀኻት/קְה֞ת) ልጅ ዹሆነው  እንበሚም(1 ዜና 6፥2) ዚመጀመሪያ ልጁ ነብይቷ ማርያም ስትሆን ሙሮ እና ወንድሙ አሮን ዚተወለዱት 1400-1500 ዓ.ዓ እንደሆነ ይታሰባል[²]። ኹዚህ ሁሉ ዘመናት በኋላ በዘመነ አዲስ ኪዳን ጊዜ ዚጌታቜንና ዚመድኃኒታቜን እናት ዚሆነቜው ቅድስት ድንግል ማርያም ኢዚሱስን እንደወለደቜ ቅዱሱ መጜሐፋቜን ይነግሚናል። መጜሐፍ ቅዱስ ዚቅድስት ድንግል ማርያምን አባትና እናት ባይጠቅስልንም ብዙ ድርሳናትና ታሪካዊ መጜሐፍት ኢዮአቄም(Joachim) እና አና(Anne) እንደሆኑ ይነግሩናል[³]።ባጭሩ ዹሙሮ እህት ነብይቷ ማርያም ጺን ምድሚ በዳ እንደሞተቜ በኊሪት ዘኍልቁ ም.20 ቁ.1 ላይ እንመለኚታለን። ቅድስት ድንግል ማርያም ኹሙሮ እህት ማርያም ጋር በማንነት ሆነ በነበሩበት ጊዜ ይለያያሉ። እንደዚህ ያክል ዚመጜሐፍ ቅዱሱን በንጜጜራዊ ትንተና ኚተመለኚትን ወደ ቁርአኑ እንለፍና ዚመሐመድን በታሪክ ላይ ዹፈጾመውን ወንጀል እንመልኚትፊመሐመድ በቁርአኑ ላይ ዚኢሳ እናት ማርያምን እና ዚነብዩ ሙሮ እና ዚአሮን እህት ማርያምን እንደ አንድ ሎት አድርጎ ማስተማሩ ነው!!!ዚብዙ ዘመናት ልዩነት ያላ቞ው በሁለት ታሪኮቜ መካኚል ያለ መመሳሰልን ማለትምፊ ➙ ዚሙሳ ወንድም ሃሩን እና ዚኢሳ እናት ወንድም ሃሩን ➙ዚሙሳ አባት ኢምራን እና ዚኢሳ እናት አባት ኢምራን ➙ ራሷ ባለ ታሪኳ ዚኢሳ እናት መርዹመ እና ዚሙሳ እህት መርዹም ያለውን መመሳሰል ስንመለኚት በይበልጥ ታሪኩን እንድንመሚምር አድርጎናል። በዚህም ጉዳይ በርኚት ያሉ ዳዒዎቜና ለእስልምናና ለመሐመድ ዘብ(ጥበቃ) እቆማለሁ ዚሚሉት ዳዕዋጋንዲስቶቜ ዚሙግት ነጥብ ይሆኑናል ብለው ዚሚሰነዝሯ቞ውን ነጥቊቜ እንመልኚትፊ ዚስም መመሳሰልፊ በዚህ ዚሙግት ነጥባ቞ው ላይ ዚኢሳ እናት ዚሆነቜው ዹመሹዹም ወንድም ሃሩንና ዚሙሳ ወንድም ሃሩን ሁለት ዚተለያዚ ማንነትና በተለያዚ ጊዜ ዚነበሩ ሰዎቜ ናቾው ይላሉ። ይሄን ዚሙግት ነጥባ቞ውን ይደግፍልናል ብለው ዚሚጠቅሱት ሐዲስ አል-ሙጊራህ ኢብኑ ሹዕባ ዚሚባል ሰው ወደ ነጅራን በሄደ ጊዜ በዛ አካባቢ ያሉ ክርስቲያኖቜ በሱሚቱል መርዹምን (19:28) ላይ ዹተጠቀሰውን « ዚሃሩን እኅት ሆይ! » ዹሚልን ጜሑፍ እንዳነበቡና ሙሳ ደግሞ ኚዒሣ ብዙ ጊዜ በፊት እንደነበር በነገሩት ጊዜ ጥያቄውን ይዞ ለመሀመድ አቀሚበላ቞ው። መሀመድም በመልሳ቞ው “ዚድሮ ሰዎቜ ኚራሳ቞ው በፊት ኚነበሩት ዚነቢያቶቜ ስሞቜ ኚነቢያቱ ህልፈት በኋላ ይጠቀሙ ነበር” ብሎ ነገሹው(ኢማም ሙስሊም መጜሐፍ 38 ሐዲስ 13)። አስተውሉፊ በሐዲሱ መሠሚት ዚመጜሐፉ ባለቀቶቜ ዚሚባሉት ክርስቲያኖቜ ስለ ኢዚሱስ እናት ዚማርያም ወንድም ስለሆነው አሮን ዚሚባል ወንድም እንዳላት በጭራሜ ዚማያውቁ እንደሆኑና አል-ሙጊራህ ኢብኑ ሹዕባ ዚሚባለው ሙስሊም ሙእሚን ግራ ተጋብቶ ጉዳዩ ጥያቄ እንደፈጠሚበት እንመለኚታለን። በተጚማሪም ዚምእመናን እናት ዚሆነቜው አዒሻ (ኡም አል-ሙእሚኒን/أمّ الم؀منين‎) እንኳን እንደማታውቅ ኚኚዓብ (ሹዐ) ጋር ባደሚገቜው ንግግር እንሚዳለን[⁎] “
’ዚሃሩን(ዚአሮን) እህት!’ (ዚሱራ 19 28) ዹሙሮን ወንድም አሮንን አያመለክትም። ዓኢሻ(ሹዐ) ለኚዓብ(ሹዐ) “ #ዋሜተሃል” በማለት መለሰቜለት። .”(ተፍሲር ኢብን ኚሲር 19:28) በእነዚህ ሁሉ ሰዎቜ ማለትም ለአንዳንድ ሙስሊሞቜ እንግዳ ዹሆነና በመሐመድ ዘመን ዚነበሩት ዚተማሩ ዐሚብ ክርስቲያኖቜ(ዚመጜሐፉ ባለቀቶቜ) ዚማዚታወቅን ታሪክ መሐመድ ኚዚት አምጥቶ ነው አሮን(ሃሩን) ዚሚባል ዚማርያም(መርዹም ) ወንድም አለ ያለን? በተጚማሪም ዚኢሳ እናት ዚሆነቜው ዹመሹዹም ወንድም ሃሩንና ዚሙሳ ወንድም ሃሩን ዚተለያዩ ሰዎቜ ናቾው ካሉን አንድ ወሳኝና አነጋጋሪ ጥያቄ መጠዚቃቜን አይቀሬ ነው በታሪክ ስለማይታወቀው ሰውዬ(ዚኢሳ እናት ዹመሹዹም ወንድም ሃሩን ተብዬው) እንደዚህ ያክል አስፈላጊና ዚኢሳ እናት መሹዹም በእርሱ እስኚምትጠራ ስላስደሚገው ሰው እንዎት ቁርአን ቜላ ብሎ አለፈው እናም ስለሱ ዚሚናገሩ ዚታሪክ መዛግብት እንዎት ልናጣ ቻልን? ወይም ደግሞ ዹሙሮ (ሙሳ) ወንድም ዹሆነውን አሮንን(ሃሩን) ዚኢሳ እናት ለሆነቜው ማርያም(መርዹም) ወንድም መስሎት እንደነበር ይሄም ደግሞ ዚመሐመድ አላዋቂነት ማለትም በታሪክ ላይ ዚሰራው ወንጀል መሆኑን ማወቅ ይጠበቅብናል። ኢኜዋህ(إِخْوَة) ዚሙሳ ወንድም እና ዹመርዹም ወንድም አንድ ማንነት ናቾው ስንል አማኞቜ ወንድም እና እህት ናቾው በሚል ቀመርና ስሌት ነው ይሉናል። ይሄም ዚሙግት ነጥባ቞ው መፍለክለኪያ(ማምለጫ) ያጣ ሰው ለማምለጫ ኚሚፈጥሚው ቀዳዳ ተለይቶ አልታዚኝ። በሃገሬው አባባል “ ኚቀዳዳ ይሻላል ጚምዳዳ ” እንደሚባለው ነጥቊቻ቞ው ዚመሐመድን ስህተት መደበቅ ሳይቜልላ቞ው ሲቀር ኚአንዱ ወደ አንዱ በይሻላል መንፈስ ይራወጣሉ። ለማንኛውም በአማኞቜ መካኚል ኢኜዋህ(إِخْوَة) ማለትም ወንድማማቜነትና እህትማማቜነት ቢኖርም አሁንም ዚሱሚቱል መርዹም(19:28) ኚጥያቄ አያመልጥም። ቁርአኑ ስለ ሙሳ ኚወንድሙ ሃሩን ይልቅ በስፋት ነግሮን ሳለ ሙሳ ሳይጠቀስ ሃሩን ዚተጠቀሰበት አግባብ ግልጜ አይደለም።ደግሞስ መርዹም አባቷ ኢምራን እያለ በሙሳ ወንድም በሃሩን ስም መጠራቷ ምንን ያመለክታል? ደግሞም በሌላ ክፍል በሱራ 33 እና 66:12 ላይ “ዚኢምራን ሎት ልጅ” በመባሏ ወደ ሱራ 19:28 ስንመጣ ኚሩቅ ዘመን ባለ ሰው ስም መጠራቷ ጉዳዩን ዹበለጠ ብዥታንና እና ቜግርን አስኚትሏል። ለዚህ ሁሉ ጥያቄ መልስ ዹሚሆነው ዚመሐመድን ስህተት መቀበል ነው። በተጚማሪም መሐመድን ለዚህ ትልቅ ስህተት ያበቃው አንዳንድ ምንጫ቞ው በቅጡ ኚማይታወቁ በክርስትናው ላይና በአይሁዳውያን መጜሐፍት ላይ ኚሚጚመሩ አፈታሪኮቜ ዹሰማውን በራሱ አገላለጜ ስለሚዘግብ ነው። ሱሚቱ መርዹም ዹተወሰኑ ክፍሎቜ ዚአፖክሪፋን ታሪኮቜ እንደ ዚያዕቆብ ፕሮቶቫንጄሊዚም (Protoevangelium of James) እና ዹሐሰተኛው-ማ቎ዎስ ወንጌል(gospel of Pseudo-Matthew) ካሉ አፈ ታሪኮቜ ዚአዋልድ ታሪኮቜ ተመሳሳይነት ያለው ታሪክ እናገኝበታለን። ለምሳሌ ዹቮምር ዛፉ ስር ዹተፈጠሹው ታሪክ[⁵] ስለ መርዹም ወላጆቜ ታሪክ[⁶] ለአብነት ተጠቃሜ ና቞ው። በተጚማሪም በአሚባዊቷ ምድር በፍልስጀም ውስጥ በቅድስት ድንግል ማርያም ዹተሰዹመ ዚባይዛንታይን ቀተክርስቲያን አለ። ይህ ቀተክርስቲያን ኚእስልምና ወግ ጋር ጥልቅ እና ዚተወሳሰበ ግንኙነት አለው እንዳለው ታሪክ ይነግሚናል። በመሐመድ ዘመን አካባቢ ይህቜ ቀተክርስቲያን ዚክርስትና አምልኮ ማዕኹል ነበሚቜ። በቅዳሎ ወቅት ኚመጜሐፍ ቅዱስ ውጭ áŠšáˆšáŠá‰ á‰ á‹ ኚካቶሊክ እና ኚኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን በተቃራኒ በዚህ ጊዜ ለንባብ ኚአፖክሪፋ እና ኚሌሎቜ ቀኖናዊ ያልሆኑ መጜሐፍት መነበቡ ዹተለመደ ነው። በተጚማሪም ዚተለያዩ ዚክብሚ በዓላት ዚምታኚብር ቀተ ክርስቲያን ነበሚቜ። ለምሳሌ ላይ በነሐሮ ወር አጋማሜ ላይ ቀን 14 ኚነብዩ ኀርምያስ ሕይወትም ኚአዋልድ መጜሐፍት ይነበብ ነበር። በምንባቡ ላይ መሐመድ በሱሚቱል በመርዹም ላይ እንዳሰፈሚው አይነት ማለትም ሃሩን(አሮን) ዚማርያም (መርዹም) ወንድም በማለት ዹተጠቀሰን ጜሑፍ እናገኛለን[⁷]ፊ “ነቢዩ [ኀርምያስም] እንዲህ አለ – መምጣቱ ለእርስዎ እና ለሌሎቜ ልጆቜ በዓለም ምልክት መጚሚሻ ይሆናል ።57 እንዲሁም ዹተደበቀውን ታቊት ኚዓለት ላይ ዚሚያወጣ ዹለም ኚማርያም ወንድም አሮን በስተቀር ።(The Lection of Jeremiah) በተመሳሳይ ሁኔታ ቁርአኑ ስለ ማርያም (መርዹም) ሲናገር ሃሩን(አሮን) ዚማርያም (መርዹም) ወንድም እንደሆነ ዘግቩልን አግኝተናል፩ 19፥28 « ዚሃሩን እኅት ሆይ! አባትሜ መጥፎ ሰው አልነበሚም፡፡ እናትሜም አመንዝራ አልነበሚቜም» አሏት፡፡ يَا أُخْتَ هَارُونَ مَا كَانَ أَُؚوكِ امْرَأَ سَوْءٍ وَمَا كَانَتْ أُمُّكِ َؚغِيًّا በመጚሚሻም ለመሐመድ ዘብ እንቆማለን ባዮቹ አብዱሎቜ ታሪክን በመደበቅ ዚመሐመድን ስህተቶቜና አላዋቂነቱን ለመደበቅ መፍጚርጚራ቞ው ዚሚያዋጣ አይደለም። መሐመድ ኚታሪክ አንጻር ሲሳሳት ይሄ ዚመጀመሪያው እንዳልሆነ ኚታሪክ መዛግብት ዘንድ ብዙ መሚጃዎቜን ስንበሚብር ዚሚጋለጥ ሐቅ ነው። እስኚምንገናኝ በክርስቶስ ፍቅር ቾር ሰንብቱ! ማጣቀሻዎቜ እና ማስፈንጠሪያዎቜ [¹] https://al-maktaba.org/book/9783/383 [²] á‹šá‰°áˆˆá‹«á‹© ዚታሪክ ተመራማሪዎቜ እና ጞሐፊዎቜ ስለ ሙሮ ዚውልደት ዘመን ላይ ዚተለያዚ አስተያዚቶቜን ሰንዝሚዋል። በአማካይ ኚወሰድነው ሙሮ እና ወንድሙ አሮን ዚተወለዱት 1400-1500  ዓ.ዓ ገደማ እንደሆነ አብዛኞቹ ምሁራን ይስማሙበታል(Seder Olam Rabbah,Jerome’s Chronicon (4th century) gives 1592 for the birth of Moses,The 17th-century Ussher chronologycalculates 1571 BC (Annals of the World, 1658 paragraph 164) [³] The gospel of the birth of Mary, 1:1-2, Gambero, Luigi (1999). Mary and the Fathers of the Church: The Blessed Virgin Mary in Patristic Thought. Ignatius Press.ISBN 978-0-89870-686-4. [⁎] https://quran.al-islam.com/Page.aspx?pageid=221&BookID=11&Page=1 [⁵] The Gospel of Pseudo-Matthew Chapter 20 [⁶] Protoevangelium of James Gospel

ማርያም ዚሐሩን እህት? Read More »

ዚመስዋዕቱ ልጅ ኢስሐቅ ወይስ ኢስማኢል?

ኢድ አል አድሃ(عيد الأضحى) ኢድ(عيد) ማለት በአል፣ ድግስ ወይም ለመታሰቢያነት ዹሚኹበር ነገር ማለት ሲሆን áŠ á‹µáˆƒ (أضحى) ወይም ቁርበን (قرؚان) ወይም ደግሞ ዚእብራይስጡ አቻ ቃል ቆርባን(קׇךְב֌֞ן) ማለት “መስዋዕት/መባ” ማለት ነው። ኢድ አል አድሃ ሁለተኛው ዚሙስሊም ወገኖቻቜን ክብሚ በአል ነው። በዚህም ክብሚ በአል ሙስሊም ወገኖቻቜን ለመስዋዕትነት ዹሚሆነውን ዚበግ፣ ዚግመል፣ ዹፍዹል ወዹም ዚጠቊትን ወዘተ ዚመሳሰሉትን ዚእንስሳትን ደምን ያፈሳሉ። ዹበአሉ እርሟ ወይም ጅማሮ በቁርአን ውስጥ ዚኢብራሂም(ዐሰ) ልጁን ለአምላኩ ለመሰዋት ዚታዘዘበትን ቀን ለማሰብ ሲባል ዹሚኹበር በአል ነው። በቁርአን ላይ አላህ በሱሚቱ አልሷፍፋት (ዚተሰላፊዎቹ ምዕራፍ) ላይ ስለ ተሰላፊዎቜ እምነት በሚናገርበት ክፍል በቁጥር 83 ላይ ኚአማኞቜ መካኚል ዹሆነው ኢብራሂም (ዐሰ) አንደኛው እንደሆነ ይናገራል። በዛው ክፍል በቁጥር 100 ላይ ደግሞ ኢብራሂም (ዐሰ) አንድን ጞሎትን ሲጞልይ እንመለኚታለንፊ As-Saffat 37:100ጌታዬ ሆይ! ኚመልካሞቹ ዹሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡(رَؚِّ Ù‡ÙŽØšÙ’ لِى مِنَ ٱلصَّلِحِينَ) ዚኢብራሂምም አምላክም ታጋሜ በሆነ ወጣት ልጅም ባሪያውን አበሰሚው። ኢብራሂም (ዐሰ) ኚባዱ ፈተና ዹሚጀምሹው በቁጥር 102 ላይ ነው። አምላኩ ዹሰጠው ልጅ ለስራ በደሹሰ ጊዜ ኢብራሂም (ዐሰ) በራዕይ አንድ ልጁን እንደሚያርድ ሁኖ ያልማል። እርሱም ለልጁ ስለ ራዕዩ ምን እንደሚያስብ በጠዹቀው ጊዜ “ዚታዘዝኚውን ሥራ” ብሎ ሲፈቅድለት እንመለኚታለን። አሁን ዋናው ጉዳይና ጥያቄ ያ ለኢብራሂም (ዐሰ) ዹተበሰሹው ዚመስዋዕቱ ልጅ ማነው? ዹሚለው ንግርት ነው! ዚዘመናቜን ዚሙስሊም ኡስታዞቜ ሜንጣ቞ውን ገትሚው በመኚራኚር በቁርአኑ ላይ ዚመስዋዕቱ ልጅ ኢስማኢል  ለማስመሰል ዹቁርአኑን አያህ ዚማይቀባቡት ነገር ዚለም። ኹሁሉም በላይ ደግሞ አጃኢብ ዚሚያስብለው ጥርት እና ጥንፍፍ ብሎ በመጜሐፍ ቅዱስ ላይ ዚተነገሚለትን ዹቃል ኪዳን ልጅ ይስሐቅን በእስማኀል ተክተውና አንሻፈው ዚመስዋዕቱ ልጅ እስማኀል እንደሆነ መጜሐፍ ቅዱስ ይናገራል ማለታ቞ው ነው። “..ዚያዙት ነገር..” እንደሚሉት አበው በእኛ ዘንድ ዚሙስሊም ኡስታዞቜ መካኚል ይሄንን ዜማ መስማቱ ዹተለመደ ነው። ሲጀመር ኡስታዞቹ ዹማይሆን ዹማይሆን ዚሙግት ነጥቊቻ቞ውን እዚሰካኩ ለሙስሊሙ ተደራሲያን እዚፈተፈቱ ሲያጎርሷ቞ው እኛንም (ዚክርስቲያኑን ማህበሚሰብ) ለማታለል መጣጣራ቞ው ሳስብ ይገርመኛል። ለማንኛውም ዚኡስታዞቻ቞ውን ድርሳነ ባል቎ት ወይም ዚአሮጊቶቜ ተሚት ዹሆነውን ዚሙግት ሐሳባትን በሁለት ጎራዎቜ ኹፍለን ስለ መስዋዕቱ ልጅ ማንነት እንመለኚታለንፊ ዹቁርአናዊ ሙግት በመጀመሪያ ኢስማኢል ነብይ መሆኑ ለመስዋዕትነት ዹተዘጋጀው ልጅ እርሱ ነው ዚሚያስብለን አንድምታ ዚለም። ምክንያቱም እንዲሁ ኢስሐቅም ነብይ መሆኑን ቁርአናቾው ይነግሹናል(Al-‘Ankabut 29:27)።[1] ስለዚህ ስለ ኢስማኢል ነብይነት መጥቀስና ማጠቃቀስ ጉንጭ ማልፋት ካልሆነ በስተቀር ለሙግቱ እንብዛም ውጀት ዚለውም። ለማንኛውም ኡስታዞቹ ያነሷ቞ውን ዋና ዋና ነጥቊቜን እንመለኚታ቞ዋለን። ቀጠሮ አክባሪው ዚዘመናቜን ዚሙስሊም አቃብያነ እምነት ነን ዚሚሉት በሱሚቱ መርዹም 54 ላይ ዹተጠቀሰውን ክፍል ኚሱሚቱ አልሷፍፋት 102 ጋር በማጣመር ዚተሳሳተ ምስስሎሜን (wrong analogy) በመፍጠር ለመስዋዕትነት ዹቀሹበው ኢስማኢል መሆኑን ለማሳዚት ሞክሚዋል። ነገር ግን በክፍሉ ላይ አውዳዊ ምልኚታ ስናደርግ ሙግታ቞ው ዚሚያስኬድ ሁኖ አናገኘውም፩ Maryam 19:54በመጜሐፉ ኢስማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበሚና፡፡ መልክተኛ ነቢይም ነበር፡፡(وَٱذْكُرْ فِى ٱلْكِتَؚِٰ إِسْمَٰعِيلَۚ إِنَّهُۥ كَانَ صَادِقَ ٱلْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَؚِّيًّا ) በዚህ ክፍል ላይ አላህ ዚኢብራሂምን ልጅ ኢስማኢልን ሲያመሰግነው እንመለኚታለን። ኢስማኢል ዚአሚቊቜ ሁሉ አባት ነበር። በተጚማሪም እርሱ ለቃለ ማሐላው እውነተኛና ታማኝ እንደነበር ዚሙስሊም ሊቃውንት ይናገራሉ።[2] ዹክፍሉን አውደ ሕታ቎ ለመሚዳት ቁጥር 55ን መመልኚቱ አስፈላጊ ነው፩ Maryam 19:55ቀተሰቊቹንም በሶላትና በዘካ ያዝ ነበር፡፡ እጌታውም ዘንድ ተወዳጅ ነበር፡፡(وَكَانَ يَأْمُرُ أَهْلَهُۥ ؚِٱلصَّلَوٰةِ وَٱلزَّكَوٰةِ وَكَانَ عِندَ رَؚِّهِۊ مَرْضِيًّا ) ኢስማኢል በጌታው ዘንድ ተወዳጅ ዚሆነበትና ኹላይ ደግሞ አላህ ኢስማኢልን እንዲያስቡ ለምእመናን ሲናገር በኢስማኢል ዚግብር ጉዳይ ሚገድ መሆኑ ግልጜ ነው። ኢስማኢል ለአላህ ለሆኑ ስራዎቜ ላይ ታማኝና አክባሪ ነብይ መሆኑን ኹክፍሉ አውድ መሚዳት እንቜላለን። እንደውም ዚእንግሊዘኛው ትርጉም ቁጥር 54ን ዹሚገልጾው “he was true to his promise” ለቃለ መሐላው እውነተኛ ወይም ታማኝ እንደሆነ በሚያሳይ መልኩ ነው። And mention in the Book, Ishmael. Indeed, he was true to his promise, and he was a messenger and a prophet./English – Sahih International (Maryam 19:54)/ በተጚማሪም ኢብን ጁሹይጅ ስለ ኢስማኢል ሲናገሩፊ “He did not make any promise to his Lord, except that he fulfilled it./ዚሚፈጜመውን ካልሆነ በቀር ኢስማኢል ምንም አይነት ቃለ መሐላ ለጌታው አይገባም “Ibn Jurayj ስለዚህ ኢስማኢል ለቃለ መሐላው እውነተኛ፣ ታማኝና አክባሪ መሆኑን ዚሱሚቱ መርዹም ቁጥር 54 አውዳዊ አንድምታው ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ቀጠሮ ኹሚለው ፍታ቎ ይልቅ ቃለ መሐላ ወይም ቃልኪዳን(promise) እንደሆነ ዹክፍሉ ዙሪያ ገባ ይነግሚናል። “ቀጠሮውን አክባሪ” ዹሚለው ኃይለቃል በተጚማሪም ዚማያስኬደው በመጀመሪያ አላህ በሱሚቱ አልሷፍፋት 102 ላይ ራዕይን ያሳዚው ለኢብራሂም (ዐሰ) እንጂ ለልጆቹ ለኢስሐቅ ወይም ለኢስማኢል ፈጜሞ አይደለም። فَلَمَّا َؚلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعْىَ قَالَ يَُؚٰنَىَّ إِنِّىٓ أَرَىٰ فِى ٱلْمَنَامِ أَنِّىٓ أَذَؚْحُكَ فَٱن؞ُرْ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰأََؚتِ ٱفْعَلْ مَا تُ؀ْمَرُۖ سَتَجِدُنِىٓ إِن ؎َآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَؚِّرِينَ ኚእርሱ ጋርም ለሥራ በደሹሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ ዚማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልኚትምፀ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባ቎ ሆይ! ዚታዘዝኚውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ኚታጋሟቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡ በተጚማሪም አላህ ዚመስዋዕቱን ቀጠሮ ዹሰጠው ለአባቱ ለኢብራሒም(ዐሰ) እንጂ ለልጁ አልነበሚም። ምክንያቱም ዚራዕዩና ዚትእዛዙ አክባሪ አባቱ እንጂ ልጁ አይደለም። በተጚማሪም በቀጠሮው ቀን ለመሰዋት ልጁን ዹወሰደው አባትዚው እንጂ ልጁ አይደለም። ስለዚህ ለመስዋዕትነት ዹተቀጠሹው ኢስማኢል ዚቀጠሮው አክባሪ ነበር ዹሚለው አንድምታ ኪስ ወለድ እንጂ አውዳዊ አለመሆኑን ለመሚዳት አያዳግትም። ዚኢብራሒም ጞሎት ሌላው ዚሙግት ነጥብ ብለው ዚሚያቀርቡት ደግሞ “ኢስማኢል/إِسْمَٰعِيْل”  ማለት “አምላክ ይሰማል” ማለት ስለሆነ ኢብራሒም ደግሞ በቁጥር 100 ላይ ወደ አላህ በጾለዹው መሰሚት ልጅን ሰጠው ዹሚል ነበር። ነገር ግን ኚአውዱ ተነስተን ስንመለኚት አላህ ለኢብራሒም በጞሎቱ መሰሚት ዹተሰጠው ልጅ ኢስሐቅ እንጂ ኢስማኢል እንዳልሆነ እንሚዳለን። ሲጀመር ኢስሐቅ(إسحاق) ወይም በእብራይስጥ ይሜሐቅ(י֎שְׂח֞ק) ደስታ፣ ሳቅ ወይም ብስራት ማለት ነው። በቁጥር 100 ላይ ነብዩ ኢብራሂም(ዐሰ) ጌታዬ ሆይ! ኚመልካሞቹ ዹሆነን (ልጅ) ስጠኝ(رَؚِّ Ù‡ÙŽØšÙ’ لِى مِنَ ٱلصَّلِحِينَ) ብሎ ኹጾለዹ በኋላፀ በቁጥር 101 ላይ ጌታውም ታጋሜ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው (فََؚ؎َّرْنَٰهُ ؚِغُلَٰمٍ حَلِيمٍ) ብሎ ሲናገር እንመለኚታለን። አስተውሉ! ዚጌታው መልስ ላይ “አበሰርነው” ዹሚለውን ቃል ኚኢስሐቅ ጋር እንጂ ኚኢስማኢል ዚስም ትርጉም ጋር ፈጜሞ ዹሚገናኝ አይደለም። እንደውም ስለ ልጁ ማንነት በዛው ሱራ በቁጥር 112 ላይ ግልጜ አድርጎ ዚብስራቱ ልጅ ኢስሐቅ እንደሆነ ይነግሹናል በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ኚመልካሞቹ ዹሆነ ነቢይ ሲሆን(وََؚ؎َّرْنَٰهُ ؚِإِسْحَٰقَ نَؚِيًّا مِّنَ ٱلصَّلِحِينَ)በተጚማሪ በሱሚቱ ሁድ 11፡69-71 ያለውን ክፍል ስንመለኚት በቁጥር 101 ላይ ታጋሜ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው ዹሚለው ንግግር ለኢስሐቅ መሆኑን ግልጜ ዚሚያደርግ ክፍል ነው። 11:69 – መልክተኞቻቜንም ኢብራሂምን በ(ልጅ) ብስራት በእርግጥ መጡት፡፡ ሰላም አሉት፡፡ ሰላም አላ቞ው፡፡ ጥቂትም ሳይቆይ ወዲያውኑ ዹተጠበሰን ዹወይፈን ስጋ አመጣ፡፡11:70 – እጆቻ቞ውም ወደ እርሱ ዚማይደርሱ መኟነ቞ውን ባዚ ጊዜ ሞሻ቞ው፡፡ ኚነሱም ፍርሃት ተሰማው፡፡ «አትፍራ እኛ ወደ ሉጥ ሕዝቊቜ ተልኚናልና» አሉት፡፡11:71 – ሚስቱም ዚቆመቜ ስትኟን (አትፍራ አሉት) ሳቀቜም፡፡ በኢስሐቅም አበሰርናት፡፡ ኚኢስሐቅም በኋላ (በልጁ) በያዕቁብ (አበሰርናት)፡፡ ኚኢስሐቅ ሌላ አካል በዚህኛው ዚሙግት ሐሳብ ላይ ደግሞበቁጥር 112 በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ኚመልካሞቹ ዹሆነ ነቢይ ሲሆን በሚለው ክፍል ላይ በኢስሐቅም ስለሚል “-ም” ዚምትለው ጥገኛ ምእላድ ኚኢስሐቅ ተጚማሪ ሌላ አካል እንዳለ ያመለክታል ዹሚል ሙግት ነው። ነገር ግን ይሄ ሐሳብ ፈጜሞ ዚሚያስኬድ አይደለም። አብዱሉ በክፍሉ ላይ ሁለት ልጅ ዚተባሉ አካላት እንዳሉ ይናገራል። ዚመጀመሪያው ታጋሜ በሆነ ወጣት ልጅም ሲሆን ሁለተኛው በኢሥሐቅ ብሎ ኹፋፍሎ እንመለኚታለን። እንደዛ ኹሆነ ዚሙግቱ ሃሳብ አጠያያቂ ይሆናል። ምክንያቱም በእርሱ ሎጂክ ኚሄድን በቁጥር 101 ላይ አላህ ለኢብራሒም ታጋሜ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው (فََؚ؎َّرْنَٰهُ ؚِغُلَٰمٍ حَلِيمٍ ) በሚለው አንቀጜ ላይ ወጣት ልጅም በሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት “-ም” ዚምትለው ምእላድ አሁንም በእነርሱ ሎጂክ ኢስማኢል ነው ብለው ኚሚያምኑት አካል ሌላ ኚእርሱ

ዚመስዋዕቱ ልጅ ኢስሐቅ ወይስ ኢስማኢል? Read More »

መሬትን ተሞካሚው ፍጡር  (“አል-ኑን/النون”)

በእስልምናው አስተምህሮት ውስጥ አፈታሪካዊ እና ተሚታዊ ኚሆኑት ታሪኮቜ መካኚል አንደኛው ግዙፉ እስላማዊው አሳ ነባሪ ( الحوت الإسلامي ፣ አል-ሁት አል-ኢስላሚ) ይሄም ፍጡር ምድርን በጀርባው እንደሚሞኚም ዚተገለጞለት  አፈታሪካዊው ፍጡር ነው፡፡ ታዳ  ይሄ እስላማዊው አውሬ/አሳነባሪ(አል-ሁት/ٱلْحُوتِ) በቁርአን ላይ “ምድር ተሞካሚ አሳ” ወይም “አል-ኑን/النون” ተብሎ ተጠርቷል። ቁርአኑ ስለዚህ ፍጡር ግልጜ በሆነ ሁኔታ አላስቀመጠልንም። በዚህም ምክንያት በአንዳንድ ዚሙስሊም ሊቃውንቶቜ መካኚል እስካሁኑ ሰአት ድሚስ ያልተፈታ ትልቅ ንትርክን ዹፈጠሹ ለዘመናዊው ሳይንስ ጥናቶቜ እንግዳና አጠያያቂ ዹሆነ ጉዳይ ነው። እኔም ስለዚህ ፍጡር ጉዳይ በስፋት በመመልኚት አንዳንድ እስላማዊ ጜሁፎቜን ማለትም ሐዲሳትን እና ዚተለዩ ተፍሲራትን እያገላበጥን ለማሳዚት ቀርቀያለሁ። ➙ ኹላይ በጚሚፍታ ለመመልኚት እደሞኚርነው “አል-ኑን/النون” በውሀ ውስጥ ኚሚኖሩ ዚአሳ ዝርያዎቜ መካኚል አንዱ ነው። በቁርአን በሱሚቱል አል-ቀለመ በአንደኛው አያት ላይ ተጠቅሶ እናገኘዋለን። ይሄንን አያት በእስልምናው ማህበሚሰብ ውስጥ እጅጉን እውቅና ካላ቞ው ዹቁርአን ተፍሲሮቜ (ኢብን-ኚሲር፣ አል-ቁርጡቢ፣ ጃለለይን እና አት-ጠበሪ) እንደሚያስሚዱን ኹሆነ “ኑን” ዚሚባለው ግዙፍ አሳ ነባሪ እንደሆነና ምድርን ዹተሾኹመ ፍጡር እንደሆነ ይነግሩናል። አል-ቀለም 68:1نٓۚ وَٱلْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَነ.( #ኑን)ፀ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮቜ) በሚጜፉት፡፡ ኢብን ኚሲር አል-ቀለም 68:1 ተፍሲርፊታላቁ ሙፈሲር ኢብን ኚሲር በተፍሲሩ ላይ ስለ ኑን ሲናገርፊ አላህ ‹ ኑን› ዚተባለውን ኹፈጠሹ በኋላ ምድር በኑን ጀርባ ላይ እንደዘሚጋ ይናገራል፡፡ ኹዛም ተሚቱ ይቀጥላል #ኑን ዚሚባለው ፍጡር ደነበሹ ወይም ተሹበሾ ይለናል። በዚህ መሀል ምድር ማሹግሹግ ወይም መንቀጥቀጥ ጀመሚቜ። አላህ ለዚህ ቜግር ሲል ተራሮቜን ፈጠሚ። እነዚህም ተራሮቜ ምድር እንዳትነቃነቅ እንደ ቜካል ቾኹላቾው ይለናል። እንደውም በቁርአን 78:7 ላይ “ ጋራዎቜንም(ተራሮቜን) ቜካሎቜ አላደሹግንምን(وَٱلۡجَِؚالَ أَوۡتَادًا)?)
”  አላህ ተራሮቜን ዹቾኹላቾው ዚመሬትን መንቀጥቀጥ ለማስተካኚል እንደሆነ ተፍሲራት ይነግሩናል(ጃላለይን, ኢብን ኚሲር ተፍሲር)። ምን ይሄ ብቻ አሁም አፈታሪካዊ ተሚቱ አላበቃም አል ባግሃዊ እና ሌሎቜ ዚሙስሊም ሙህራኖቜ እንደተናገሩት በዚህ ዓሣ ጀርባ ላይ ውፍሚቱ ኹሰማይና ኚምድር ዚሚበልጥ ትልቅ ዓለት አለ፡፡ ኹዚህ ዓለት በላይ ደግሞ አርባ ሺህ ቀንዶቜ ያሉት ኮርማ ቆሟል፡፡ በዚህ ኮርማ ላይ ሰባቱ መሬቶቜና በውስጣ቞ው ዚሚገኙት ሁሉ ተቀምጠዋል ብለው ያስባሉ። እስቲ ይሄን ታሪክ ኚኢማም ኢብን ኚሲር ተፍሲር በተወሰነ መልኩ እንመልኚትፊ “ ኚዚያም አላህ ‹ኑን› ዚተባለውን ኹፈጠሹ በኋላ ሰማይ ዚተፈጠሚበት ጭስ እንዲወጣ አደሚገ፡፡ ኚዚያም ምድር በኑን ጀርባ ላይ ተዘሚጋቜ፡፡ ኚዚያም ኑን ስለደነበሚ ምድር ማሹግሹግ ጀመሚቜፀ ነገር ግን (አላህ) ምድርን እንዳትንቀሳቀስ አድርጎ በተራሮቜ ቞ኚላት  “ኢብን አቡ ኑጃኢህ እንደተናገሚው ኢብን አቡ በኪር በሙጃሂድ እንዲህ ተብሎ ተነግሮት ነበር፣ “ኑን ኚሰባቱ መሬቶቜ በታቜ ዹሚገኝ ታላቁ አሣ እንደሆነ ይነገራል፡፡” በተጚማሪም አል ባግሃዊ (አላህ ነፍሱን ያሳርፋትና) እንዲሁም ሌሎቜ ሐታ቟ቜ እንደተናገሩት በዚህ ዓሣ ጀርባ ላይ ውፍሚቱ ኹሰማይና ኚምድር ዚሚበልጥ ትልቅ ዓለት አለ፡፡ ኹዚህ ዓለት በላይ ደግሞ አርባ ሺህ ቀንዶቜ ያሉት ኮርማ ቆሟል፡፡ በዚህ ኮርማ ላይ ሰባቱ መሬቶቜና በውስጣ቞ው ዚሚገኙት ሁሉ ተቀምጠዋል፡፡ ”[1] ኑን ለሚለው ቃል ትርጓሜ ሲያስቀምጥ ደግሞ “
ኑን ዚሚባለው ትልቅ አሳነባሪ ነው(Nun is a big whale/Ù†Û€ حوت ع؞يم)
” በማለት ኢብን ኚሲር ትንታኔውን አስቀምጧል።[2] አል-ቁርጡቢ ተፍሲር 68:1 Ù†Û€> الحوت الذي تحت الأرض الساؚعة>”
<ኑን>ኚሰባተኛው(الساؚعة) መሬት(الأرض) በታቜ(تحت) ዹሚገኘው አሳ ነባሪ(الحوت) ነው
.”[3] በአል-ቁርጡቢ ተፍሲር መሰሚት ” ኑን” ዚሚባለው ኚሰባተኛው  መሬት በታቜ ዹሚገኝ አሳ ነባሪ እንደሆነ ይነግሚናል። ልብ በሉ “ ኚሰባተኛው(الساؚعة)
” ሰባት ምድር እንዳለም ኹላይ በኢብን ኚሲር ተፍሲር ላይ ተመልክተናል። እነርሱም ተደራራቢ እንደሆኑ “ታሐት(تحت)” ወይም “ኚታቜ/ኚስር” ዹሚለው ቃል ያስሚዳናል። ተፍሲር አት-ጠበሪ 68:1አት-ጠበሪ በሱሚቱል አል-ቀለም 68:1 ላይ ማብራሪያ ሲያስቀምጥ እንዲህ ብሏልፊ“ هو الحوت الذي عليه الأرَضُون ”“ ሰባቱ ምድሮቜ ዚተቀመጡበት ፍጡር አሳ ነባሪ(الحوت) ነው
”[4] በእስልምናው ኮስሞሎጂ መሰሚት አላህ ሰባት ሰማያትን እንደፈጠሚ ሁሉ ሰባት ምድሮቜንም ፈጥሯል(Quran 65:12)። እነዚህም ጠፍጣፋ ምድሮቜ በአሳ ነባሪው ላይ ተደራርበው ተቀምጠው እንደሚገኙ ጥንታዊ ዚሙስሊም ሊቃውቶቜ ይነግሩናል። ተፍሲር አል-ኚቢር(አር-ሹዚ)/tefsir Al kabir(by Ar-Razi)ፊ “ ؚالحوت الذي على ؞هره الأرض وهو في ؚحر تحت الأرض السفلى ” በዚህም ተፍሲር ላይ በጀርባው ምድር ዹሚሾኹመው ዓሳ ነባሪ እንደሆነና አል-ኚቢር እዚህ ዓሳ ነባሪ ጀርባ ላይ ሚዛናዊ ዹሆኑ ጠፍጣፋ መሬቶቜ እንዳሉ  ይነግሚናል፡፡[5] ተፍሲር አል-ቃዲር/Tafsir Al-Qadir (by Shawkani) ተፍሲር አል-ቃዲር/Tafsir Al-Qadir (by Shawkani) ይህ ተፍሲር ኹ 18 ኛው ክፍለዘመን ጀምሮ ዓለም ዓሳ ነባሪ ጀርባ ላይ ተሾክሟል ዹሚል ሀሳብን በመደገፍ ያሚጋግጣል። “
.ምድርን ዹተሾኹመው ፍጡር አሳ ነባሪ/الحوت ነው
..”/Fath Al-Qadir on 68:1__[6] ሐዲስ ኚኢብን አባስ (ቱርጁማን ኡል-ቁርአን/ترجمان القرآن)(ሐዲስ ኚአት-ጠበሪ) ኢብን አባስ እንደተናገሚውፊአላህ ዹፈጠሹው ዚመጀመሪያ ነገር ብእርን  ስለነበሚ “ጻፍ!” አለው፡፡ እናም እስኚ ሰዓቱ (ዚፍርድ ቀን) ድሚስ ምን እንደሚሆን ጜፏልፀ ኚዚያም ኑንን ኹውሃ በላይ ፈጠሹ ኚዚያም ምድርን በእርሱም ላይ ተጫነቜ፡፡(ታሪኜ አት-ታባሪ) [7] ይህም ሀዲስ(ትሚካ) በሀዲሳት ሰንሰለት  ትክክለኛ(ሰሒህ/صحيح) ትሚካ ተደርጎ ተቆጥሯል፡፡[7] መሐመድ ለኢብን አባስ ዱዓ (ጞሎት) ስላደሚገ አላህም ዹቁርአንን ትክክለኛ አተሹጓጎም ያስተምሚው ነበር፡፡እንዲሁም ኢብን አባስ (ቱርጁማን ኡል-ቁርአን/ترجمان القرآن) “ዹቁርአን ተርጓሚ” ተብሎ ተጠርቷል ፣ ምክንያቱም ስለ ራእዮቜ ትርጓሜ (ቃል በቃል መተርጎም) ዚሚሰጥና ጥልቅ ዕውቀት ያለው ሰው ነበር። ኢብኑ ዐባስ (ራአ) እንደተናገሩትፊነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) አቅፈውኝ “አሏህ ሆይ! ዚመጜሐፉን (ቁርአን) እውቀት አስተምሩት ፡፡ ”(ሳሂህ ቡኻሪ 9:92:375) ታድያ ይህ በቁርአን ጥልቅ እውቀት ያለው አሊም ተራራዎቹ በቁርአን ውስጥ እንደ ቜካል እንዎት እንደተደሚጉ ዚእርሱ ትሚካ ያስሚዳል፡፡ ምክንያቱም በባህላዊው እስላማዊ ዚኮስሞሎጂ መሠሚት ምድር ኚዓሣ ነባሪው ጀርባ ላይ ትነቃነቅ (ትንቀጠቀጥ) ስለነበሚ አላህ ምድርን ዓሣ ነባሪው ላይ ተሚጋግታ እንድትቀመጥ ተራሮቜን እንደ ቜካል እንዳደሚጋ቞ው በግልጜ ሁኔታ ተርኮልናል፡፡ በመጚሚሻም ኹዚህ ሁሉ መሚጃዎቜና ማስሚጃዎቜ ዚምንሚዳው ነገር ቢኖር አላህ ሰባት መሬቶቜን ፈጥሮ በአሳ ነባሪው(“አል-ኑን/النون” ) ጀርባ ላይ ደራሚቊ በማስቀመጥ ኹዛም አሳ ነባሪው(“አል-ኑን/النون” ) ሲደነብር መሬት እዳትነቃነቅ በተራሮቜ በመቾኹል እንድትሚጋጋ አድርጓል። ይባስ ብሎም በዚህ ዓሣ ጀርባ ላይ ውፍሚቱ ኹሰማይና ኚምድር ዚሚበልጥ ትልቅ ዓለት አለ፡፡ ኹዚህ ዓለት በላይ ደግሞ አርባ ሺህ ቀንዶቜ ያሉት ኮርማ ቆሟል፡፡ በዚህ ኮርማ ላይ ሰባቱ መሬቶቜና በውስጣ቞ው ዚሚገኙት ሁሉ ተቀምጠዋል ብለው በማሰብ ይህ ለሳይንስና ለእውነታ ሆድና ጀርባ ዹሆነን ነገር ኚአንዳንድ ዹመሰለኝን ልናደርግ ኹሚሉ ፈላስፋዎቜ ቀጥታም ሆነ ተጚማምሮበት ዚተቀዳ አፈታሪክን ዹአምላክ መገለጥ ነው ብሎ መቀበል በጣም ሞኝነት ነው። አንዳንድ ዹዘመኔ ዚሙስሊሙ ማህበሚሰብ ስኮላሮቜና ዳኢዎቜ ይሄ ነገር አልዋጥ ሲላ቞ው ዚውሞት ዚትሚካ ሰነድ ወይም አምላካዊ ንግግር ዹሆነ ሀሳብ አይደለም ይሉናል።[8] ነገር ግን አይኑ ዹፈጠጠ በድሮ ዘመን በነበሩት ዚእስልምና ሊቃውንቶቜ መካኚል ተቀባይነትን ያተሚፈ ታሪክ እንደሆነ ኚተፍሲራትና ኚሐዲስ ለመመልኚት ቜለናል። ይሄን ዹመሰለ ተሚትና አፈታሪክ ታቅፈው ነው እነ ዶክተር ዛኪር ናይክና ቢጀዎቹ ቁርአን ኚሳይንስ ጋር አይጣሚስም ዚሚሉን። በመሰናበቻዬም አንድ ነገር ተናግሬ ልደምድምፊ እውነት ቁርአን ዚፈጣሪ ንግግር ነውን? ኚሆነስ ለምን ኹሐቅና ኚሳይንስ ጋር ላይስማማ ሊጣሚስ ቻለ? እውነትን ፈልጉ እውነትም አርነት ያወጣቜኋል። ማጣቀሻዎቜና ማስፈንጠሪያዎቜ [1] Tafseer Ibn Katheer;Online Edition: http://quran.al-islam.com/Tafseer/DispTafsser.asp?l=arb&taf=KATHEER&nType=1&nSora=68&nAya=1 [2] https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=0&tTafsirNo=7&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [3] https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=1&tTafsirNo=5&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [4]  https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=1&tTafsirNo=1&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [5]  https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=1&tTafsirNo=4&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [6] https://altafsir.com/Tafasir.asp?tMadhNo=1&tTafsirNo=9&tSoraNo=68&tAyahNo=1&tDisplay=yes&UserProfile=0&LanguageId=1 [7]  https://hdith.com/?s=%D8%AB%D9%85+%D8%AE%D9%84%D9%82+%D8%A7%D9%84%D9%86%D9%88%D9%86+%D9%81%D9%88%D9%82+%D8%A7%D9%84%D9%85%D8%A7%D8%A1%D8%8C+%D8%AB%D9%85+%D9%83%D8%A8%D8%B3+%D8%A7%D9%84%D8%A3%D8%B1%D8%B6+%D8%B9%D9%84%D9%8A%D9%87 [8]  https://islamqa.info/en/114861

መሬትን ተሞካሚው ፍጡር  (“አል-ኑን/النون”) Read More »

ዚቀድሞ ነብያት ክርስቲያን አልነበሩምን?

ለሙስሊም ሰባኪያን ሙግት ምላሜ ዚእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል ዹሆነው መጜሐፍ ቅዱስ ጌታቜንና መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ በሥጋ ዹተገለጠ አምላክ መሆኑንና ኚእርሱም በፊት ዚነበሩት ነብያት እና ዚእምነት አባቶቜ ኹዛም በመቀጠል በሐዲስ ኪዳን ዚነበሩት ሐዋርያቶቜ እርሱን እንደተኚተሉ ዚክርስትና መሠሚት እምነት ዹሆነው መጜሐፍ ቅዱስ ያስተምራል። በተጻራሪው ግን ቅዱሳት መጻሕፍት ተጜፈው ኹተጠናቀቁ ኚብዙ መቶ ዓመታት በኋላ ዚመጣው እስልምና ደግሞ በቀድሞ ነቢያት ተወርቶ እና ተሰብኮ ዚማይታወቅ አምላክ አስተዋወቀንፀ ኹዛም አልፎ ተርፎ ተኚታዮቹ ሙስሊም እንጂ ክርስቲያን አይደሉም ብሎ ብቻውን ቆሞ á‹«áˆµá‰°áˆáˆ«áˆá¢ ኢስላም ናቾው እንጂ ክርስቲያን አይደሉም ዹሚለው ንግግር በብዙ ሙስሊሞቜ ዘንድ እንደ ትልቅ ርዕስ አድርገው ክርስቲያኖቜን ጋርም በጥያቄ መልክ ሲቀርብ ይስተዋላል። እኛም ይህን አስተምሮታ቞ው ኹሆነው ኚቁርኣን ዹመነጹ እና ጥያቄያ቞ው በራሱ ማስሚጃ ዹሌለው ኪስ ወለድ ሙግት ሀሳብ መሆኑን እንመለኚታለን። በመጀመሪያ ግን ክርስቲያን እና ደቀመዛሙርት ማለት ምን ማለት ነው? ክርስቲያን(ΧριστιαΜούς/ክሪስትያኑስ)ፊ ማለትም ዚክርስቶስ ተኚታይ ወይም በክርስቶስ ህግ እና ትምህርት ዚሚመራ ማለት ነው። ዚእርሱ አቻ ቃል ዚክርስቶስ ደቀመዝሙር/ΌαΞητής  ሲሆን ጥቅልል ትርጉሙ “ ዚክርስቶስ ተማሪ ”ወይም” ዚክርስቶስ ተኚታይ” ማለት ነው። ዚሐዋርያቶቜ ደቀመዝሙር ዚነበሩት ኹማን እግር ስር እንደተማሩ ለመግለፅ ይህንን ቃል ይጠቀሙትም ነበር። ለቅምሻ ታህል ደቀመዝሙር በሚለው ቃል ላይ አንድ ምሳሌ ላሳይፊ ጶሊቃርጶስ በ70ዓ.ም ተወልዶ በ155 ዓ.ም ወይም በ160 ዓ.ም ዹሞተ ዚሐዋሪያው ዮሐንስ ደቀመዝሙር(ማ቎቎ስ/ΌαΞητής) እንደነበር ዚቀተክርስቲያን ዚታሪክ መጻሕፍት ያወሱናል። በተጚማሪ ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአ቎ንስ ደግሞ ስሙም በሐዋ17:34 ላይ ዹተጠቀሰ ሲሆን ይህ ዚቀተክርስቲያን አባት ደግሞ ዚሐዋርያው ጳውሎስ ደቀመዝሙር (ማ቎቎ስ/ΌαΞητής) እንደነበር ይነገራል። ይህ ማለት ጶሊቃርጶስ ዚሐዋርያው ዩሐንስ ተኚታይ ሲሆንፀ ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአ቎ንስ ዚቅዱስ ጳውሎስ  ደቀመዝሙር እንደሆነና ዚአስተማሪያ቞ው ማ቎቎ስ ተብለው መጠራታ቞ውም ኚታሪክ ክታባት እንሚዳለን። በአንዳንድ ዚሙስሊም ተሟጋ቟ቜ ዚኢዚሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርት እንዲሆኑ እንጂ ክርስቲያን እንዲሆኑ ኢዚሱስ ሐዋርያትን አላዘዘም ይላሉ። ነገር ግን ዚክርስቶስ ደቀመዝሙር ማለት እና ክርስቲያን ኹሚለው ቃል ጋር ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ ደቀመዛሙርቮ ካለ( ዮሐ 15:8፣ 13:35፣ ማር 14:14፣ ሉቃ 22:11፣ ማቮ 26:18
) ዚእርሱ ተኚታይ(ክርስቲያን) መሆናቾውን ምንም ሳናቅማማ እንቀበላለን ማለት ነው። ስለ ክርስትና እና ደቀመዝሙር ይህን ያህል ካዚን ነብያቱ ክርስቲያን ነበሩ ወይ? ክርስቲያን ኚነበሩስ ምንድነው ማስሚጃቹ? ዹሚለውን በመመለስ እንዝለቅ። ዚክርስቶስ ምስክርነት በማ቎ዎስ ወንጌል 5፡3-13 ላይ በተለምዶ ይህ ክፍል ዚተራራው ስብኚት በመባል ዚሚታወቅ ሲሆን ሙሉ ዐውደ ምልኚታ እያነበባቹ ስትወርዱ ቁጥር 11-12 ላይ አንድ አስደናቂ ንግግር እንመለኚታለን እንዲህ ይላል፩ “ሲነቅፉአቜሁና ሲያሳድዱአቜሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሞት ሲናገሩባቜሁ ብፁዓን ናቜሁ።”  ማ቎ዎስ 5፥11 እዚህ ክፍል ላይ ኢዚሱስ እርሱን በመኹተላቾው ስለሚደርስባ቞ው ነቀፌታ፣ ስደትና ቜግር ሁሉ መፍራት እንደሌለባ቞ውፀ ጚምሮም ብፁዓን እንደሆኑ ይነግራ቞ዋል። ስደቱም በክርስቶስ ያለ መሆኑን በቁጥር 11 ላይ በእኔ ምክንያት ዹሚል ንግግር ያስቀምጣል። በዚህም አላበቃም ይቀጥልና በቁጥር 12 ላይ እንዲህ ይለናል፩ “ዋጋቜሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላቜሁ፥ ሐሎትም አድርጉፀ ኚእናንተ በፊት ዚነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋ቞ዋልና።”  ማ቎ዎስ 5፥12 ክርስቶስን ዹሚኹተሉ ሰዎቜ ዋጋቾው ታላቅ እንደሆነ! እርሱንም መኹተል ዹዚህ ስደት እና እንግልት ኚንቱ እንዳልሆነፀ ይልቁንም “ኚእናተ በፊት ዚነበሩትን ነብያቶቜ እንዲሁ አሳድዷ቞ዋልና በማለት በሚኚቱን ይነግራ቞ዋል። ምክንያቱም በክፍሉ ዐውድ ሲብራራ እነርሱ ተነቅፈዋል፣ ያላ቞ው ነገር አጥተዋል፣ ስለ እርሱ ሲሉ መሚባ቞ውን ጥለው ተኚትለውታል መሠደዱ እና ማጣቱ “በእኔ ምክንያት ነው ይላቾዋል” ነገር ግን እኔን መኚተላቜሁ ኚንቱ አይደለምፀ ብሎ ይቀጥልናፊ ኚእናተ በፊት ዚነበሩትን ነብያት እንዲሁ አሳድዷ቞ዋልና በማለት ኚቀድሞ ነብያት ጋር አገናኝቶት ዚቀድሞዎቹም መሠደዳ቞ው በእርሱ መሆኑን ይነግራ቞ዋል። በተጚማሪም በማ቎ዎስ ወንጌል ምዕራፍ 23፥34-37 ላይ ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚኊሪት ህግ መምህራንን እና ፈሪሳውያንን ሲነቅፍ እንዲህ ብሎ ሲናገር እንመለኚታለንፊ ማ቎ዎስ 23 ³⁎ ስለዚህ፥ እነሆ፥ ነቢያትንና ጥበበኞቜን ጻፎቜንም ወደ እናንተ እልካለሁፀ ኚእነርሱም ትገድላላቜሁ ትሰቅሉማላቜሁ፥ ኚእነርሱም በምኵራባቜሁ ትገርፋላቜሁ ኹኹተማም ወደ ኹተማ ታሳድዳላቜሁፀ³⁵ ኚጻድቁ ኚአቀል ደም ጀምሮ በቀተ መቅደስና በመሠዊያው መካኚል እስኚ ገደላቜሁት እስኚ በራክዩ ልጅ እስኚ ዘካርያስ ደም ድሚስ በምድር ላይ ዹፈሰሰው ዚጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባቜሁ ዘንድ።³⁶ እውነት እላቜኋለሁ፥ ይህ ሁሉ በዚህ ትውልድ ላይ ይደርሳል።³⁷ ኢዚሩሳሌም ኢዚሩሳሌም ሆይ፥ ነቢያትን ዚምትገድል ወደ እርስዋ ዚተላኩትንም ዚምትወግር፥ ዶሮ ጫጩቶቜዋን ኚክንፎቜዋ በታቜ እንደምትሰበስብ ልጆቜሜን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳቜሁምም። ትኩሚት ሰጥታቹ ተመልኚቱፀ ቅዱሱም ማ቎ዎስ ዚክርስቶስን ንግግር አጜንዖት ሰጥቶ ነው እዚጻፈልን ያለው። ዚጌታቜን ዚኢዚሱስ ንግግርም ዝም ብሎ ሀይለ ቃል አይደለም ይልቁን ዚርዕሳቜን ዋና ማገር እንጂ። እንዲህ ነው ነገሩፊ ጌታቜን እሱን ባለመቀበላ቞ው ዚኢዚሩሳሌም ነዋሪዎቜ በራሳ቞ው ላይ ሊደርስባ቞ው ያለውን መኚራ ተናግሯል ነገር ግን ኹዛ መኚራ ያርፉ ዘንድ ዶሮ በክንፎቿ ስር እንደ ምትሰበስብ ሲጠራ቞ው እንመለኚታለን። á‰ á‹›á‹ ክፍል ላይ፩ “እኔ ወደ እናንተ ነቢያትን እልካለሁ” ስለዚህ ያለ ጥርጥር እዚህ ነብያትንን፣ ሐዋርያትን እና ሌሎቜ ዚእሱን ተኚታዮቜ መሆኑን እዚገለፀ ነው። á‹­áˆ… ማለት ምን ማለት ነው? በድጋሚ ወደ ማ቎ዎስ ተመልሳቹ ጌታቜን ዹተናገሹውን እና ያለውን አስተውሉፊ “ኚአቀል እስኚ ዘካሪያስ” ስለ አቀል ሞት ተጜፎ ዹሚገኘው በዘፍ 4፥8 ላይ ሲሆን፣ ስለ ዮዳሄ ልጅ ስለ ዘካሪያስ ሞት ደግሞ በ2ዜና 24፥20-22 ተጜፏል። ጌታቜን ኢዚሱስ በዚህ ላይ ምን እያለ ነው ኚተባለ በአይሁድ ዚቅዱሳት መጻሕፍት ቅደም ተኹተል መሠሚት፣ መጜሐፈ ዜና መዋዕል ዚብሉይ ዚመጚሚሻ መጜሐፍ ነው። “ኚአቀል እስኚ ዘካሪያስ” ዹሚለው አባባል እኛ “ኚዘፍጥሚት እስኚ ራዕይ” ኹምንለው ጋር ተመሳሳይ ነው። ታዲያ ጌታቜን ይህን ሀይለ ቃል መጠቀሙ ዚብሉይ አጠቃላይ ሰማዕታን ዹሆኑ መልዕክተኞቜ እርሱ እንደላካ቞ው ማስገንዘቡን እንመለኚታለን። አስተውሉ እኔ ልኬ ነበር ገደላቜሁ እያላ቞ው ነው። ዚትኛው ነብይ እንዲህ ሊናገር ይቜላል? ለዚህም ነው ኚጌታቜን ንግግር ተነስተን ኢዚሱስ ያህዌ ነው፣ ዚቀድሞም ነብያት እርሱን ሲኚተሉ ነበር ዚምንለው። ዚእነዚህ ክፍል ማብራሪያ ኚሌሎቜ ቅዱሳት መጜሐፍት ጋር በማመሳኚር ኚእነርሱ(ኚሐዋርያቶቹ) በፊት ዚነበሩት ነቢያትና ዚእምነት አባቶቜ ጚምሮ ክርስቶስን እንደተኚተሉ ስለ እርሱም ሲሉ መኚራን እንደተቀበሉ እናም እንደተነቀፉ ኹዚህ በመቀጠል በቅድመ ተኹተል እንመለኚታለን። ዚሌሎቜ ሰዎቜ ምስክርነት ቅዱሳት መጻሕፍት ኹዚህ ርዕስ አንፃር ምን ያስተምራሉ? ዹሚለውን ለመመለስ በዕብራውያን መልዕክት ምዕራፍ 11:1-40 ያለውን መመልኚት ለዚህ ጥያቄ ጥሩ ምላሜ ዹምናገኝ ይሆናል። በዚህ ዚታሪክ ምዕራፍ ስለ እምነት አባቶቜ ኚሚያወሳ ክፍል ኹሆነው ዕብራውያን ምዕራፍ 11:25-26 ዹሙሮ ያሳለፈው ዚህይወት ውጣውሚድ እንዲህ እንዲህ በማለት ያስቀምጣልፊ “ኚግብፅም ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ ዚሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቊአልና ለጊዜው በኃጢአት ኹሚገኝ ደስታ ይልቅ ኚእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መኚራ መቀበልን መሚጠፀ ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና።”  — ዕብራውያን 11፥25-26 በደንብ አስተውሉ ዹዚህን ክፍል ጥቅስ ኚማ቎ዎስ ወንጌል 5:11-12 ጋር ስናነፃፅሚው ጥልቅ መልዕክት ይነግሚናል። ኹላይ በተራራው ስብኚት ላይ እርሱን በመኹተል ስለሚደርስ መኚራ ኚነገራ቞ው በኋላ በዚህም ሳያበቃ እነርሱ ብቻ ሳይሆኑ በእርሱ ምክንያት መኚራው ዚበዛባ቞ው ዚቀድሞም ነቢያቶቜም ጭምር በመኚራ ውስጥ ማለፋቾውንና ዹቀኝ እጃ቞ውን አሻራ አሳርፈው እንዳለፉ ይነግሚናል። ታዲያ ኚቀድሞ ነብያት ውስጥ ታላቁ ነቢይ ዹነበሹው ሙሮ <<ኚግብፅ ጮማ እና ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መኚራን መቀበል>> እንደመሚጠ ዚዕብራውያን መጜሐፍ ይነግሚናል። ስለዚህ ክርስቲያን በሚለው ዹቃሉ ትርጓሜ መሠሚት በመነሳት ኚቀድሞ ነብያት ውስጥ ሙሮ ክርስቲያን ማለትም ዚክርስቶስ ደቀመዝሙር (ΌαΞητής/ማ቎቎ስ) እንደነበሚ እንመለኚታለን ማለት ነው። ታዲያ ታላቁ ዚብሉይ ኪዳን ነቢይ ሙሮ እንዎት ሆኖ ነው ክርስቶስን ተኚትሎ ሙስሊም ዹሚሆነው? ሙስሊም ማለትስ ክርስቶስን መኹተል ነውን? መልሱን ለአንባቢ ልተወው። ዚዕብራውያን መልዕክት ጾሐፊ በዚህ አላበቃም ተጚማሪ ጥልቅ ጠቢብ ሚስጥር እንዲህ በማለት ለተደራሲያኑ ይገልፅላቾዋል፩ “እነዚህም ሁሉ በእምነታ቞ው ተመስክሮላ቞ው ሳሉ ዹተሰጠውን ዚተስፋ ቃል አላገኙም፥ ያለ እኛ ፍጹማን እንዳይሆኑ እግዚአብሔር ስለ እኛ አንዳቜ ዚሚበልጥ ነገርን አስቀድሞ አይቶ ነበርና።”  ዕብራውያን 11፥39-40 እነዚህ ሁሉ ዚተባሉት በቁጥር 38 ላይ በጠቅላላ ለመተሹክ ጊዜ ያጥሚኛል ያላ቞ውን መሆኑን በክፍሉ ዐውደ ምንባቀ ላይ መሚዳት ይቻላል። ኹላይ ባለው ጥቅስ በመጚሚሻ ቁጥር ስር

ዚቀድሞ ነብያት ክርስቲያን አልነበሩምን? Read More »

Scroll to Top