FAQ

የባሕርዩ ምሳሌ

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አንድ ሙግት መልስ ፈልጋለሁ በሚል ርዕስ አንድ ጥያቄ ተቀምጦ ነበር። ይኼም ሙግት ኢየሱስ ፍጡር ነው ከሚል ከአንድ አርዮሳዊ በተለምዶ የይሖዋ ምሥክሮች ቤተ ጎራ እንደሚመደብ ጥያቄውን ያነበበ ሰው ወዲያውኑ ያውቃል። ኢየሱስ ፍጡር ነው ያለውም ከዚህ ጥቅስ የተነሳ ነበር፦ “እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤”  — ዕብራውያን 1፥3 ምሳሌ ሲባል ሰው በእግዚአብሔር ምሳሌ ተፈጥሯል እናም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ምሳሌ ነው። ስለዚህ ፍጡር ነው የሚል ድምዳሜን አስቀምጦም ነበር። መልስ ምሳሌ የተባለበት ምክንያት ኢየሱስ በትክክል አብን የሚገልጥ መሆኑን ለማመልከት እንጂ ፍጡር መሆኑን ለማሳየት አይደለም፡፡ ኢየሱስ የእግዚአብሔር አብ ምሳሌ መኾኑ የተጠቀሰበት አምላክነቱን ለክርክር ሊቀርብ በማይችልበት ኹኔታ የሚገልጥ ሌላ ጥቅስ በዕብራውያን መልዕክት ውስጥ ይገኛል(ዕብራውያን 1፥2 ዕብራውያን 1፥8 እና ሌሎችም)። ከጠያቂያችን ጥቅስ ግን ተነስተን በአጭሩ መልስ እንስጥ፡- “እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤”  — ዕብራውያን 1፥3 “የባሕርዩ ምሳሌ” ተብሎ የተተረጎመው “ሁፖስታሴዎስ ካራክቴር” የሚል የግሪክ ሐረግ ሲሆን ካራክቴር የአንድን ነገር ትክክለኛ፣ ያልተሸራረፈ፣ ከዚያኛው አካል ያላነሰ፣ እኩል የሆነ ማንነት የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ “ምሳሌ” ከዚያኛው አካል ጋር በኹሉም ረገድ ፍጹም ተመሳሳይ ነው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የሚነግረን ወልድ ከአብ ልዩ መኾኑን፤ ነገር ግን ደግሞ ከአብ ጋር ፍጹም እኩል መኾኑን ከምንም ዓይነት ጥርጣሬ በፀዳ ኹኔታ የሚገልጥ ክፍል ነው፡፡[፩] ስለዚህ ይሄ ክፍል ኢየሱስ ፍጡር ነው ተብሎ የቀረበው መለኮታዊ ባሕርዩን ገላጭ እና ይልቅም አምላክነቱን የሚያሳይ ሆኖ እናገኘዋለን። ማጣቀሻ [፩] Vines Complete Expository Dictionary of Old and New Testament Words, Thomas Nelson Publishers, Nashville Camden New York, 1984, P. 319.

የባሕርዩ ምሳሌ Read More »

መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን እንጠያየቅ – ክፍል 2

ጥያቄ፦ እሺ ይሄን ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ያልከውን እንደ ሙግትህ ልቀበልህና መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ እየተባለ የተለያየ ሥነ-አፈታት ላይ የተለያየ ምልከታ ትደርሳላችሁ? ለዚህ ስነ አፈታት ዳኛችሁ ማነው? መልስ፦ በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው። ይሄ እኮ ጥያቄ ቢነሳ በእናተም ዘንድ ያለ ነው።(ትውፊት ያላችሁ እናተም ይሄንን ተመሳሳይ ክሌም ማንሳት እንችላለን።) እኛ ነገሩን ሥነ መለኮታዊ ክፍፍሎሽ(Theological Triage) ብንሰራለት እንኳን። ወደፊት የማስረዳህ ይሆናል። አሁን ግን ወደ ጥያቄህ መልስ ልለፍልህ። ጥያቄ፦ እሺ መልስ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ እያላችሁ ሥነ አፈታት ላይ ብዙ ትለያያላችሁ። የሚል ጥያቄ ነው የተነሳው። ያው የሥነ-አፈታት መርሖ በመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ መነጸር ሲታይ የራሱ የሆነ መንገድን አለው። ለሶላ ስክሪፕቹራ አማኝ መጠየቅ የሌለብህና ማሶገድ ያለብህ ጥያቄ፦ ስህተት1፦ እንደው ሰው እንደፈለገ እየፈታ እየተረጎመ መጠቀም አለበት የሚል እሳቤ አለው። ስህተት2፦ የመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ችግር ይሄን ያስከትላል። ስህተት1 እና ስህተት2፦ የሁለታችሁ ዳኛችሁ ማነው ታዲያ? ለስህተት1 እና ለስህተት2 ድምዳሜህ ምላሻችን፦ መልስ፦ እነዚህ ነገሮች ለመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ አማኝ ለሆነ ሰው የሚቀርብ ጥያቄ ነው ብዬ አላምንም።[እንዴት የሚለውን ወደ በኋላ እናየዋለን] ታዲያ ለዚህ መነሾ የመጀመሪያው መፍትሄ መርሕ የምንለው የሥነ አፈታት መርሖ በመባል ይታወቃል። ይህ ደግሞ አንደኛው መንገድ ነው(አውዳዊ ንባብ ንፅፅራዊ ምልከታ ነው።) ጥያቄ፦ ቆይ ቆይ ይህንን ታዲያ ሌላኛው ጎራም እነሱም ክሌም ያደርጉታል ግላዊነት አይደለም ወይ? መልስ1፦ ጥሩ ጥያቄ ነው። ግን የተሳሳትከው ነገር በተለይ በተለይ HGL(ጽሑፋዊ፣ ሰዋሰዋዊ እና ታሪካዊ ዳሰሳ) እንደነ ዲኤ ካርሰን የመሳሰሉ ምሑራን ይህ አይነቱ ትርጓሜ መጠቀም ይበልጥ ከግላዊነት ይልቅ ወደ ጽኑ ትርጓሜ እንደሚያመጣ ያስረዳሉ። ምክንያቱም ይሄ አይነቱ መንገድ ሥነ አፈታቱ በአውዱ ሲታይ፦ ➙ አውዳዊ ያልሆነው ተሟጋችህ ይወድቃል ➙ ከዛም ሻገር ስትል ሰዋሰዋዊ መንገድ በመጠቀም ታርመዋለህ፣ ➙ታሪካዊ መንገድን ትጠቀማለህ። ይሄ አይነቱ ሥነ አፈታት ለግላዊነት ወጥመድ ነው ማለት የማይቻልበትን መንገድ ቀጣይ ከማነሳቸው ካልኩህ ጋር አያይዤ አቀርባቸዋለሁ። መልስ 2፦ ሌላው በእነ R.C Sproul እና John Piper ተቀባይነት ያለው ሲሆን ይህህም መንፈሳዊውን ትርጓሜ ነው። ይሄ የሚወሰደው በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ነው። እንደ R.C Sproul እና John Piper አይነቱ የሚሉት መንፈስ ቅዱስ ለመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ እንዳንስት ትልቁን ሚና በአማኞች ዘንድ ከጥናት አንጻር እንደሚሰራ ይናገራሉ። ➙ ታሪካዊ የጉባኤዎች ውሳኔ እና መግለጫዎች ለሥነ አፈታት ቀጥተኛ ተዛምዶ ባይኖራቸውም(ማለትም በእነርሱ ተጠቅሞ በቀጥታ መተርጎምን ማድረግ ባይችሉም) በሉተራኑ ሥነመለኮቱ ላይ ባሉ እንደነ Robert Kolb እንደሚሉት ክሪዶች እና ኮንፌሽኖች ለመጽሐፍ ቅዱስ ስነ አፈታት አቅጣጫ ጠቋሚዎች ናቸው ይላሉ። ይህም ለቅዱሳት መጻሕፍት የበላይ ባለሥልጣንነት እንዲሁም በቂ እንደ መረታዊ አስተምህሮ ማለታችንም ነው። መልስ 3፦ በሥነ አፈታት ላይ ጥያቄህን በመራሕያነ ተሐድሶዎች በኩል ዘንድ የሚነሱ ሙግቶች ቢሆኑ ለምሳሌ፦ ካልቪኒዝም እና አርሜኒያን የሚል ቢሆን በቀላሉ ከትውፊት ጋር ካልሆነ የምትሉም ራሳችሁ ተከፋፍላችሁ ሳለና ወደ አበው ጎራ መካከል ጠጋ ስንል ራሱ ከሥነ አፈታት ጀምሮ ሁለት አይነት ቤተ እውቀቶች አሉ ብሎ ሀሳብህን መሞገት ይችላል። ምክንያቱም በእስክንድርያ ያለው ቤተ እውቀት እና አንጾኪያ ያለው ቤተ እውቀት መካከል የሥነ አፈታት ልዩነቶች ይስተውላሉ። የእስክንድርያው አመስጥሮታዊ ፍቺ(allegorical interpretation) ሲጠቀም የአንጾኪያው ደግሞ ቁማዊ(literal) ይጠቀማል። በተለይ በነገረ ክርስቶስ ዶክትሪን አንጻር ከተመለከትነው ጎራ መደብ ልዩነቶች ይስተዋላሉ(Hypostatic Union & two nature of Christ)። የእኛ ጥያቄ የሚሆነው ስለዚህ የትኛው የትምህርት ቤተ እውቀት መጽሐፍ ቅዱሳዊውን ስነ አፈታት ተጠቅሟል? የሚባል ጥያቄ ቢነሳ በቀላሉ የሚታለፍ አይደለም።[ማንሳትም እንችላለን ለማለት ነው] ስለዚህ መልስ1፣ መልስ2 እና መልስ3 ሲቀመጡ፦ ድምዳሜ 1፦ ከላይ እንዳልነው በእኛ ምሑራን ዘንድ የሚባለው የቅዱሳት መጽሐፍ ትርጓሜ ከማንኛውም ግላዊነት የጸዳ መሆን ይኖርበታል። ነገር ግን በቤተክርስቲያን ታሪክ ስንመለከተው ሁለቱ ቤተ እውቀቶች ተጽዕኖ ያሳደረባቸው የየራሳቸው ነገሮች አላቸው። የእስክንድርያው ቤተ እውቀት(Alexandria school) ለምሳሌ በፕላቶኒዝም በሃይል የተጠቃ ሆኖ እናየዋለን። ለዚህም የእስክንድርያው አርጌንስ ስለ ነብስ የሚያብራራው ከባሲል ቄሳርያው ሊለይ ይችላል(የተለየም ነው) አርጌንስ ስለ ነብስ ያለውን ቴዎሪ ለጥጦ ፕላቶኒክ በሆነ መልኩ መጽሐፍ ቅዱስን መፍታትን ሊያደርግ ይችላል። ይሄም ደሞ ምናልባት ወደ ስህተት ሊያመጣውም ይችላል(ስለ soul የሰጠውን ኮንሰፕሽን ስለምናውቀው) ስለዚህ ነው ያለንበት አካባቢ ያስተማሩን ሰዎች ወይም የግል ምልከታ በራሱ ለመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ አፈታት መርህ ሆነው ይመጣሉ።[እንደውም የአበውን ሥልጣን ከመጽሐፍ ቅዱስ እኩል ካደረግነው ግላዊ ሥነ-አፈታት ሚነግስ አይደመስልህም?] ስለዚህ አንድ ትክክለኛ የሆነ የሥነ አፈታት መርሖ ያስፈልገናል። ይህም ሁሉም የሚዳኝበት HGL የምንለው መርህ ላይ አይመስልህም? ያው እንደ ጥያቄ ከተነሻ መወያየት እንችላለን ለማለት ነው። ድምዳሜ 2፦ ስለዚህ በሥርአት ከተጠናና ቋንቋውን እና ታሪካዊ አውዱ ከታየ ወደ ትክክለተኛው ሥነ አፈታት ይመራናል። መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ምንም እንኳን ግላዊን ትውውቅ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ያለንን ሕብረት ቢያበረታታም ከትርጓሜው እጅጉን ያርቀናል ማለት አይደለም። ስለዚህ በዶክትሪናል ነገሮች ሆኑ በአንዳንድ ውይይቶች ቤተክርስቲያን ውስጥ መታቀፍና ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመተርጎም አማኞች ተጠያቂ ቢሆኑ የሚልን ነገርን መርሳት የለብንም። ይሄም ደሞ ግላዊነትን ይቀንሳል። በተለይ እንደ አማኝ አጥብቀን መያዝ ያለብን መንፈሳዊው ላይ ነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ለአማኞች የተላከው ለማስተማር ለማቅናት እና አቅጣጫን ለመስጠት እንደሆነ ሁሉ በጸሎት እና በትጋት በህብረትም ሆነ በግል በቤተ ክርስቲያን ጥላ ውስጥ የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ ጠቃሚ ነው እንላለን። ይህም የመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ አስተምህሮን አይቃረንም።

መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን እንጠያየቅ – ክፍል 2 Read More »

መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን እንጠያየቅ – ክፍል 1

ጥያቄ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን(Sola Scriptura) ተቀብሎ መቀጠል የቤተክርስቲያን ሥልጣናዊነትን እና የአበውን ጽሑፍ ባለስልጣንነትን እንዳንቀበል ያደርጋል። አይደል? መልስ፦ ኧረ በፍፁም! ይህን እንድንል ትንሽ ክፍተት እንኳን አይሰጠንም። ምክንያቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ብቻና አይሳሳቴው ባለስልጣን ነው የሚለው አስተምህሮ እነዚህን ጨምሮም ነው፦ ➙ ቤተክርስቲያን ባለስልጣን ነች። ➙ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ስንልም የአበው ክታባት ባለስልጣን አድርገን ነው። ይህን ስንል ግን ሊሳሳት የማይችልና የሁሉ መመዘኛ ባለስልጣን የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ መሆኑን አምነን ነው። ለዚህም ነው አውግስጢኖስ እንዲህ በማለት የተናገረው፦ If you discover in my writing anything false or blameworthy, you may know that it is bedewed by a human cloud, and you may attribute that to me as truly my own.[1] ስለዚህ እነዚህ መጻሕፍት ማለትም የአበው ክታባት ሕጸጽ ከሌለባቸው (infallible & inerrant) ከሆኑ ከቅዱሳት መጻሕፍት ቀጥሎ ክብር የሚሰጣቸው መጽሐፍት ናቸው። ጥያቄ፦ ለዚህ ንግግርህ የአዲስ ኪዳን ድጋፋት አለህ? መልስ፦ አዎ። ጌታ ኢየሱስ ካደረገው እና ካስተማረው ማሳየትና መጥቀስ ችላለሁ። ለምሳሌ፦ ማቴዎስ 23¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¹ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብሎ ነገራቸው፦² ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል። ጌታችን በማቴዎስ 23:2-3 በሙሴ ወንበር ላይ ስላሉ ጻፎችና ፈሪሳውያን ለተናገሩት ቃል ለቃላቸው መታዘዝ እንደሚገባ ያስተምራል።(ይሄም ደሞ በዘመኑ ሥልጣናዊ መሆናቸውን ያሳያል። ለዛም ሥልጣን መታዘዝ እንዳለብን ይናገራል።) ይህን አይተን ረሱ ጌታችን በማቴዎስ ምዕራፍ 15፥1-39 ላይ ጻፎች እና ፈሪሳውያን የደነገጓቸውን መመሪያዎች ከዋናው ከመጽሀፍ ቅዱስ ማዕከላዊ ትምህርት ጋር ስለተቃረኑ ይቃወማቸዋል።(ይህ ደሞ በመጀመሪያው ክፍለ ዘመናት ከመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን በላይ የሆነ ግዛት እንዴሌለ ያሳየናል። መልሴን በአጭሩ ሳስቀምጠው፦ መነሻ1፦ ጻሕፍት እና ፈሪሳውያን ሥልጣናዊ ናቸው። መነሻ2፦ ይህ አንድ አካል ሥልጣን አለው ማለት ግን የግድ ሊሳሳት የማይችል ሥልጣን(ከመጽሐፍ ቅዱስ እኩል የሆነ) ነው ማለት ግን ፈጽሞ አይቻልም። ስለዚህ ድምዳሜ1፦ ስለዚህ ይህ ሥልጣናዊው አካል ራሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ይመዘናል። ልክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳደረገው። ድምዳሜ2፦ እነዚህ መዛኞቹ ጌታችንን ራሱ የጠየቁት እና የመዘኑት በመጽሐፍ ቅዱስ መሆኑ የሚያሳየው በዘመኑ በእነርሱ አስተሳሰብ መጽሐፍ ቅዱስ የበላይ ባለስልጣን መሆኑን ጥቂት የሚያሳይ ፍንጭ ነው። በዚህ ክፍል ግን ጌታችን የበላይ ባለስልጣን ያደረገው ራሱ በነብያቱ በኩል የተናገረውን የራሱን ቃል በሕዝቡ ዘንድ ነው። በመጨረሻም ድምዳሜ1 እና ድምዳሜ2፦ መጽሐፍ ቅዱስ የማይመዘን መመዘኛ ነው። ይህ ማለት ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ማለት ነው። አንተም ስትጠይቅ እኛ የምንለውን መጽሐፍ ቅዱስ ባለሥልጣን ነው ስንል ሌሎች ባለስልጣናንነታቸውን መካድ ማለት አይደለም። ይልቅ የማይመዘነው ብቸኛ የማይሳሳት መመዘኛ መጽሐፍ ቅዱስ ነው ማለት ነው። መልስ፦ እሺ። አሁን የእኛን እሳብ ተረዳህ? ጥያቄ፦ ይቀጥላል… ማጣቀሻ Augustine, Letter 19 (To Gaius):

መጽሐፍ ቅዱስ ብቻን እንጠያየቅ – ክፍል 1 Read More »

Scroll to Top